ሐሙስ 26 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፲፰ ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን #ለቅዱሳት_ደናግል_አጥራስስ_ወዮና እና #ለቅዱስ_ፊልጶስ_ሐዋርያ፣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፰ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፰ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮና ሰማዕተ #ቅዱሳት_ደናግል_አጥራስስ_ወዮና።

✍️፩-ኅዳር ፲፰ በዚህች ዕለት #ቅዱሳን_ደናግል_አጥራስስ_እና_ዮና በሰማዕትነት አረፉ።

  + እሊህም ቅዱሳን በአንድነት ሰማዕትነትን የተቀበሉት በዚህች ዕለት ነው። ቅድስት አጥራስስ ጣዖታትን ለሚያመልክ ንጉሥ ለእንድርያኖስ ልጁ ስትሆን አዳራሽ አሠርቶ ከማንም እንዳትገናኝ አድርጎ ለብቻዋ አኖራት። እርሷ ግን ስለዚህ ዓለም ከንቱበት ታስብ ነበርና በልቡናዋ ቸሩን አምላክ ትፈልግ ስለነበር እውነተኛውን ጎዳና ይመራት ዘንድ የእውነት በተመስጦ ትለምነው ነበር። ከልመናዋም ጽናት የተነሳ አንድ ቀን በራእይ "ወደ ፍላጽፍሮስ ልጅ ወደ ድንግሊቱ ዮና መልእክት ላኪ፣ እርሷ የእግዚአብሔርን መንገድ ትመራሻለች" የሚላትን አየች። ስትነቃም በልቧ እጅጉን ደስ ተሰኘች።

  + መልእክተኛም ልካ ድንግሊቱን የፍላጽፍሮን ልጅ የሆነችውን ቅድስት ዮናን አስጠራቻት። እርሷም ስትመጣ ከእግሯ በታች ሰገደችላትና እውነተኛውን መንገድ ታስተምራት ዘንድ ለመነቻት። ቅድስት ዮናም ደስ በመሰኘት የቀናውን የሃይማኖት መንገድ ታሳያትና ትገልጥላት ገባች። የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነበትን ምክንያት ከቀዳሜ ፍጥረት ቅዱስ አዳም ድቀት ጀምራ ስለሰብዓ ትካት ጥፋትና በንፍር ውኃ መጥፋት፣ ከዚያም የጥፋት ውሃ ስምንት ነፍሳት ስለመትረፋቸው፣ ከጥፋት በኋላ ስለሕዝብ መብዛትና ስለተምልኮ ጣዖት መስፋፋት፣ አበ ብዙኃን ቅዱስ አብርሃም ስለመጠራቱ  . . እያለች ስለትንቢተ ነቢያት እና ስለቸሩ ጌታችን መገለጥ ስለመከራ መስቀሉ፣ በመጨረሻም ስለስሙ ሲሉ መከራ የሚቀበሉት እንደምን ያለ ድንቅ ክብር እንደሚያገኙ ነገረቻት። በዚህም ቅድስት አጥራስስ በጌታችን ስም አመነች። 

  + ይህ ኹሉ ሲደረግ ግን አባቷ አያውቅም ነበር። በኋላ አባቷ ሊድራት ስለወደደ ልጄ ከመሞሸርሽ በፊት ለአምላካችን ለአጵሎን ዕጣን አሣርጊ አላት። እርሷ ግን መልሳ አባቴ የነፍስህና የሥጋህም ጌታ እያለ ስለምን በእሊህ ጠፊ ከንቱ ጣዖታት ነፍስህን ትጎዳለህ አለችው። አባቷም እንዲህ ያለውን ነገር ከርሷ በመስማቱ ተደንቆ ማን ልቡናዋን እንደለወጠ ሲያጣራ የፍላጽፍሮን ልጅ ድንግሊቱ ዮና መኾኗን ሰማ። እርሱም ተቆጥቶ ጉድጓድ አስቆፈረና እሳት እጅግ አድርጎ አስነደደ። ኩለቱም የንገሥታት ልጆች ነበሩና ከልብሳቸው አላራቆቷቸውም፣ ነገር ግብ ስለነርሱ መሞት ያዘኑ ኹሉ እንዲህ ካለው ምክራቸው ለጥቂት እንዲተዉ እሊህን ቅዱሳን ለመኗቸው። እንርሱ ግን ስለስሙ መከራን ለመቀበል በጥብዓት ቆርጠዋልና ወደኋላ ከቶ አላሉ። እሳቱም ከጉድጓዱ ወጥቶ ሲንቀለቀል፣ እሊህ ኹለት ደናግልን እጅ ለእጅ እንደተያያዙ ጨመሯቸው። ወደ ምሥራቅም ዞረው ረጅም ጸሎትን ከጸለዩ በኋላ ነፍሳቸውን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ። 

  + እሳቱም ስንኳን ሰውነታቸውን ልብሳቸውን አለመንካቱን የተመለከቱ ኹሉ እጅግ አደነቁ። ምእመናንም ቅዱስ ሥጋቸውን ወስደው የመከራው ዘመን እስኪያልፍ በክብር አኖሯቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በእሊህ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን፣ በረከታቸውም እጽፍ ድርብ ኹኖ ይደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለዮና መጽሐፈ ክርስቶስ መጽሐፋ
ወለአጥራስስ ሱታፋ
በእንተ ሃይማኖት ርትዕት ወበእንተ ጽኑሕ ተስፋ
ሶበ ተወርዋ አሐቲ እደ ካልዕታ ሐቂፋ
ማዕከለ እሳት ኅቡረ አዕረፋ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ከንዑዳን ክቡራን አንቅዕት ንጹሐን ከኾኑ ከዐሥራ ኹለቱ ሐዋርያት አንዱ #ቅዱስ_ሐዋርያ_ፊልጶስ በሰማዕትነት የሞተበት መታሰቢያው ነው።

  + ይህ ቅዱስ የሚያስተምርበት ዕጣው ወደ አፍራቅያ እና ወደ አውራጃዋ ኹሉ በሆነ ጊዜ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በውስጧ ሰበከ። እነርሱንም ድንቆች ተአምራትንም ጭምር አድርጎ ወደ ቀማች ሃይማኖት ከመለሳቸው በኋላ ወደ ሌላ አገር ሔዲ የከበረ ወንጌልን ማስተማር ጀመረ። ከእነርሱም ብዙዎች ያመኑ ሲኖሩ ያላመኑት ግን በንጉሡ ለመወደድ ብለው ሊገድሉት ይወዱ ነበር። ይዘውትም ጽኑዕ ሥቃያትን አሠቃዩት፣ እርሱ ግን ይሣለቅባቸው ነበር፣ ስለምን የነፍሳችሁን ድኅነት አታስቡም? ይላቸው ነበር። እነርሱ ግን ብዙ ካሠቃዩት በኋላ ዘቅዝቀው ሰቀሉት፣ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። ሥጋውንም በእሳት ሊያቃጥሉ ቢሉ የእግዚአብሔር መልአክ ኹላቸውም እያዩት መጥቶ የቅዱስ ፊልጶስን ሥጋ ወሰደባቸውና ከኢየሩሳሌም አገር ውጪ አግብቶ ሠወረው። ኹሉም ይህን ተአምራት እንዳዩ ከቅዱስ ፊልጶስ አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብለው አመኑ።

  + ሥጋውም ይገለጥላቸው ዘንድ ሦስት ቀንና ሌሊት ከጦሙ በኋላ በሦስተኛው ቀን ተሰጥቷቸዋል። እነርሱም በቸሩ እግዚአብሔር አመኑ፣ ከሥጋውም ብዙ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ፣ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በአባታችን በቅዱስ ሐዋርያ ፊልጶስ ጸሎት ይማረን፣ በረከቱም እጽፍ ኹና ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ከሮሜ አገር #ቅዱስ_ኤላውትሮስና #እናቱ_ቅድስት_እንትያ በሰማዕትነት አረፉ።

  + ይህም ቅዱስ እግዚአብሔርን የሚፈራ አንቂጦስ ከሚባል ኤጲስ ቆጶስ ዘንድ ዲቆና ተሾመ፣ ደግሞ በዐሥራ ስምንይ ዓመቱ ቅስና ተሾመ። ከዚህም በኋላ በሃያ ዓመቱ አላሪቆስ ለሚባል አገር ጵጵስና ተሾመ። በዚያም ወራት ንጉሥ እንድርያኖስ ወደ ሮሜ አገር መጣ፣ ስለኤላውትሮስም በሰማ ጊዜ ይዞ ያመጣው ዘንድ ፊልቅስ የተባለውን የጦር አለቃውን ላከው። እርሱም ሲኼድ ቅዱስ ኤላውትሮስን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምር አየው፣ በትምህርቱም አመነና የክርስትናን ጥምቀት ተጠመቀ።

  + ኤላውትሮስም ከንጉሡ ፊት እንደቀረበ ንጉሡ "ስለምን ተሰቅሎ ለሞተ ሰው ባሪያ ትሆናለህ፣ ራስህን ነጻ ለምን አታደርግም" አለ እየዘበተ። ቅዱስ ኤላውትሮስም መልሶ ነጻነትስ ያለ በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል እንጂ በሌላ በምንም አይደለም አለው። ንጉሡም ትቆጥቶ የእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመረው። ነገር ግን የእሳቱ መንኰራኲር ራሱ ተቆራርጦ ወደቀ፣ እሳቱም ጠፋ። ይህም ንጉሥ በቅዱስ ኤላውትሮስ ላይ የሚያደርግበትን ነገር ቢያጣ ምን እንደሚያደርግ እስኪያስብ ወደ ወህኒ ቤት ጣለው። በወህኒም ሳለ የገነት ዖፍ መብልን አመጣችለትና በልቶ ጠገበ። ቆሊሪቆስ የተባለውም መኰንን ይህን በማየቱ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ። 

  + ከዚህም በኋላ ፈረሶችን አምጥተው በሠረገላ ላይ እንዲጠምዷቸው፣ ቅዱስ ኤላውትሮስንም ከሠረገላው በታች አሥረው ሕዋሳቱ እስኪሰነጣጠቅ ፈረሶችን እንዲያስሮጡአቸው አዘዘ። በዚህም ጊዜ መልአከ እግዚአብሔር ከተፍ አለና ያንን ማሠሪያ ፈትቶ ቅዱስ ኤላውትሮስን ከፍተኛ ተራራ፣ አራዊት የሚኖሩበት ቦታ አደረሰውና በዚያ ተወው። ቅዱስም እግዚአብሔርን እያመሰገነ በዚያ ሲኖር ንጉሡ እንድርያኖስ ለአደን ወታደሮቹን ቢልክ ወታደሮቹ ቅዱሱን አገኙትና ወደ ንጉሡ አቀረቡት። ንጉሡም ለአናብስት ሰጠው፣ አናብስቱ ግን መጥተው ላበቱን ላሱለትና ተደፍተው ሰገዱለት፣ ተመልሰው ግን ከአረማውያን ወገን የሆኑ ሰዎችን መቶ ሃምሳ የሚሆኑ ገደሉ። ንጉ

ሡም በዚህ እጅጉን ተቆጥቶ ኹለት ወታደሮችን አዘዘና ቅዱስ ኤላውትሮስን እና እናቱን ቅድስት እንትያን በጦር ወግተው እንዲገድሏቸው ኹለት ወታደሮ

ችን አዘዘ። እናቱም የልጇን አንገት እንዳቀፈች ወግተው ገደሏቸው። እነርሱም የድል የሰማዕትነትን አክሊል ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በእሊህ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን፣ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለፊልጶስ ጽዑረ አባል በመቅሠፍት
ወለኤላውትሮስ ርጉዝ በብልሐ ኲናት
ምስለ እንትያ እባእ ኀበ ተርህወ ገነት
ያሩጸኒ መዓዛሆሙ ወጼናሆሙ ዕፍረት
ለዝ ሐዋርያ ወለዝ ሰማዕት።

✍️፬-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የየዋህ_አትናቴዎስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ለእግዚአብሔር ነአኲቶ በእንቲአከ መቅድመ
ወናተሉ ካዕበ ለኂሩትከ ሰላመ
አትናቴዎስ የዋህ እንተ ኢተአምር ቆመ
መፍትው እንበይነዝ ይስምዩከ ስመ
ስቴ ሠናየ ወእክለ ጦዑመ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱሳት አጥራስ ወዮና ደናግል ሰማዕታት ወቅዱስ ፊልጶስ ሐዋርያ ወበእንተ ቅዱስ ኤላውትሮስ ወእንትያ እሙ ወበእንተ ቅዱስ አትናቴዎስ የዋህ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

t.me @deaconmelakuyifru

የኅዳር ፲፯ ዝክረ ቅዱሳን

❤️እንኳን #ለመምህረ_ኲሉ_ዓለም_ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ እና #ለቅዱስ_ሲኖዳ_አበምኔት፣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።❤️

የኅዳር ፲፯ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፯ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮነ ፍልሰተ ሥጋሁ #ለቅዱስ_መምህረ_ኲሉ_ዓለም_ዮሐንስ_አፈወርቅ።

✍️፩-ኅዳር ፲፯ በዚህች ዕለት የዓለም ኹሉ መምህር የኾነው የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሥጋው ፍልሰት ተደረገ።

 ❤️+ ስለዚህ ታላቅና ግሩም ቅዱስ ምን መናገር ይቻላል በእውነት?! የኔታ እንዲህ አሉ፣ " ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን በትክክል ለመግለጥ ራሱን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅን መኾን ያስፈልጋል!"። በአማን አፈወርቅ ዘአልቦቱ ምሳሌ፣ #ሙሐዘ_ትርጓሜያት #ወሊቀ_ሊቃውንት #አፈ_በረከት #አፈ_መዐር #አፈ_ዕንቊ #አፈ_ጳዝዮን #አፈ_ርኄ . . #መምህረ_ኲሉ_ዓለም ነው።

 ❤️ + እንግዲህ የዚህ ታላቅ ቅዱስ ዜና እንደኔ ባለው ጎስቋላ ስለተነገረ እንዳያዝንብኝ ይቅርታውን እና የርሱንም እርዳታ እየጠየቅሁ ለበዓሉ ማዘከሪያ እጅግ ጥቂት ብቻ እላለሁ። አፈ ወርቅ የተባለውን የቊስጥንጥንያውን ኮከብ ብሩህ ቅዱስ ዮሐንስን በምን ቃል እንገልጠው ይሆን?! 

  ❤️+ ይህ ቅዱስ አባቱ አስፋኒዶስ (ሴኮንዶስ) ሲባል እናቱ ደግሞ አንቱዛ (አትናስያ) ትባላለች። ደገ'ኛ ክርስቲያኖች ናቸው። የተወለደው በ፫፻፵፱ዓ.ም ሲኾን አባቱም ገና በልጅነቱ በማረፉ እርሱን የማሳደጉ ድካም በእናቱ ላይ ኾነ። ቅዱስ ዮሐንስ ከዓለሙ የፍልስፍና ጥበብም ኾነ ሕግ ያልተማረው ምንም ምን አልነበረም። እንዲያውም መምህሩ ክርስቲያኖች ነጥቀው ባይወስዱብን ኖሮ እኔን የሚተካው እርሱ ነው ብሎ እስኪተማመንበት ድረስ ድንቅ ዕውቀት ከማስተዋል ነበረው። 

  ❤️+ ከዚህም ኹሉ ዓመታት በኋላ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተማረ። ቅዱስ አባታችን ማር አፈወርቅ ዮሐንስ ለቅዱሳት መጻሕፍት እና ለማንበብ የነበረው ፍቅር እጅግ ልዩ ነው። እጅግ ይወደውም የነበረ አንድ ደግ ባልንጀራው የኾነለት ባስልዮስ የሚባል ደግ ባልንጀራ ነበረው። እርሱ እና የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እናት በሊቁ ሕይወት ትልቅ ቦታ አላቸው። ቅዱስ ዮሐንስ ለመመንኰስ በወደደ ጊዜ እናቱ ከእርሷ ጋራ እንዲኖር ስለወደደች እርሷ እስክታርፍ ድረስ ራሱን የትሕርምትን መንገድ እያለማመደ አብሮአት ቆየ። እርሷም ስታርፍ የነበረውን ሀብት ንብረት ኹሉ ለድኆች መጽውቶ እጅግ ጥብቅ የኾነውን የትሕርምት ሕይወቱን የሚያደርግበትን ቦታ ለይቶ ወደ በረሓ ወጣ። በዚያም ከባልንጀራው ከቅዱስ ባስልዮስ (ይህኛው ባስልዮስ፣ ባስልዮስ ዘቂሣርያ አይደለም ሌላ ነው) ጽኑዕ ገድልን ሲጋደል ከመኖሩ የተነሳ ከጨጓራ ሕመም ጀምሮ በብዙ ይሠቃይ ነበር። 

 ❤️ + ቅዱሱ አባታችን ሊቀ ሊቃውንት መምህረ ኲሉ ዓለም አፈወርቅ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲተረጉም ዲያቆን እያለ ብሉያትን ቅስና ከተቀበለ በኋላ ደግሞ ሐዲሳትን ተርጉሞአል። ከዚያም በኋላ ያስተማራቸውን ትምህርቶች ዘርዝሮ ማን ይጨርሳቸዋል? እርሱ ከድውያን ጋር እንደሐኪም ኹኖ፣ ከሙሽሮች ጋር ልክ ሙሽራ እንደሚኾነው ኹኖ ከመነኩሳትና ከባሕታውያን እንደባለ ጽኑዕ ገድል ተሐራሚ መነኰስ ባሕታዊ ኾኖ፣ ከወጣቶች ጋር እንደወጣት ከአዕሩግ ጋር እንደአዕሩግ፣ ከፈላስፎች ጋር እንደታላቅ ሊቅ ፈላስፋ ብቻ ከኹሉም ጋር እንደሚመቸው ኹኖ ሲያስተምር ያየው ሰው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ታላቁ አባታችን አንድ ሰው ነው ብሎ መጥራት ይቸግረዋል። እርሱ ለኹሉም እንደሚስማማው አድርጎ ማስተማር ያውቅበታል። (ይህን ድንቅ ሊቅ መምህር የሰጠን አባታችን እግዚአብሔር ይክበር ይመስገን!!)

 ❤️+ ቅዱስ ዮሐንስ ከትምህርቱ ጣዕም የተነሳ በኹሉ እጅግ ይወደድ ነበርና ዘወትር ትምህርቱን ለመስማት ኹላቸውም አይጠግቡትም። እርሱም ድርሳናትን የመድረስና የመተርጎም የቅዱሳት መጻሕፍት ኹሉ ጸጋ ያደረበት ገና በዲቁና ሳለ ነበር። ከጊዜም በኋላ የቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳሳት ሲያርፍ ንጉሡ አርቃዴዎስ ቅዱስ ዮሐንስን እጅግ ይወደው ነበርና ለምን እንደሚወሰድ እንኳ ሳያውቅ ወደ ቊስጥንጥንያ አስመጥቶት በ፫፻፺፯ዓ.ም ሊቀ ጵጵስና ተሾመ። 

❤️ + ሊቀ ጳጳሳት ከኾነም በኋላ በሚያስተምራቸው ትምህርቶቹና ተግሣጻቱ እጅጉን የሚወደድ ነበርና ከትምህርቱ ጣዕም የተነሳ "አፈወርቅ" ተብሎ ተጠራ። ዳግመኛም ንጉሡ የ"ኢያዕመራ እስለ አመ ወለደት ወልደ ዘበኲራ"ን ትርጓሜ እንዲያስረዳው ቅዱስ ዮሐንስን ቢጠይቀው እርሱ በመለሰለት ድንቅ መልስ ምክኗት የእመቤታችን ሥዕለ አድኅኖ እየዞረችው "ሠናየ ተናገርከ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሠናየ ተናገርከ ዮሐንስ ልሣነ ወርቅ" ብላዋለችና ይህን ሰምተው ዮሐንስ "አፈወርቅ" አሉት። ቅዱስ ዮሐንስ አባታችን ድርሳናቱን ልብ ብሎ ላስተዋለው ሰው ተዋሕዶን በሚገባ የሚሰብክ ቅዱስ ነው። ይኸውም ሊታወቅ ድርሳናቱ ኹሉ በጎ የኾኑ የምስጢራት መፍሰሻ ሲኾኑ ከዚሁ አሠናስሎ ደህሞ ወደ ሕይወት የሚተረጎሙ የምግባራትን ነገር ይጽፋል። ስለዚህም የቅዱስ ዮሐንስ ድርሳናትን ልዩ ከሚያደርጋቸው ነገሮች አንዱ ድርሳናቱ ኹለት ክፍል አላቸው። አንደኛው የትርጓሜ ወይም ሀተታ ክፍል ሲኾን ሌላኛው ደግሞ የምግባር ክፍል ነው።

 ❤️+ እርሱ እውነተኛ መምህር ነው፣ መምህር ዘበአማን ወመገሥፅ ዘኢያደሉ ለገጽ- ፊት አይቶ የማያደላ እውነተኛ መገሥጽ፣ ነገሥታትን የማይፈራ በድኃው የማይመካበት እውነተኛ ቅዱስ ነው። በዚህም የተነሳ ነው ዕረፍቱ የኾነው። ይህም እንዲህ ነው፣ ቅዱስ ዮሐንስ አንድ ቀን ንግሥቲቱ አውዶክስያ የአንዲትን ድኃ ሴት ቦታ በመውሰዷ ልትመልስላት እንደሚገባ አጥብቆ ነገራት ገሠጻትም። አልሰማም ባለችውም ጊዜ አወገዛት፣ ከቅዱስ ቊርባንም ለያት። ይህም ስላስቆጣት እርሱ በምግባር ጉድለትና በምንፍቅና ካወገዛቸው ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ኾና ወደ ደሴተ አጥራክያ አጋዘቸው። ከስደትም ከተመለሰ በኋላ ዳግመኛ አጋዘቸውና በስደት ሳለ "ስለኹሉም ነገር ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን" ብሎ ግንቦት ፲፪ ዕለት በክብር አረፈ። ንግሥቲቱ አውዶክስያም ይህን ታላቅ ቅዱስ በማሳደዷ አልተጠቀመችበትም፣ በጭንቅ ደዌ ተቀስፋ አርፋለች።

❤️ + ቅዱስ ዮሐንስ ካረፈ ከሠላሳ አምስት ዓመታት በኋላ በታናሹ ቴዎዶስዮስ ዘመነ መንግስት የሥጋው ፍልሰት ኾኗል። ይህም የሆነው ፓትርያርኩ ቅዱስ ጵሮክለስ ስለቅዱስ ዮሐንስ ሲያስተምራቸው በሕይወቱ እጅግ ከመደነቃቸው የተነሳ ሳያስጨርሱት እባክህን አሁኑኑ ቅዱስ ዮሐንስን አምጣልን ብለውታል። በዚህም የሥጋው ፍልሰት ኾኗል።

 ❤️ + ቅዱስ ዮሐንስ ሕይወቱ ትምህርቱ፣ ትምህርቱ ሕይወቱ የኾነ ድንቅ ምድራዊ መልአክ ሰማያዊ ሰው፣ ሊቅ መምህር ወመገሥጽ ዘኢያደሉ ለገጽ፣ ኃያል ተሐራሚ መነኰስ፣ ድንቅ መንፈሳዊ መተርጉም ነው። ቤተ ክርስቲያናችንም ይህን አፈወርቅ ወዕደ ወርቅ ቅዱስ ዮሐንስን ስትጠራው፥
   √አፈ ዕንቊ
   √አፈ መዐር
   √አፈ ርኄ
   √አፈ ሶከር
   √አፈ አፈው
   √ልሣነ ወርቅ
   √አፈ በረከት፣ ርዕሰ ሊቃውንት
   √ሐዲስ ዳንኤል
   √መምህረ ኲሉ ዓለም
   √መምህር ወመገሥጽ ዘኢያደሉ ለገጽ እያለች ነው።

  ❤️+ይህም ሊቅ ለቅዱስ ጳውሎስ የነበረው ፍቅር ልዩ ነው። ስለርሱ ስንቱን እንዘረዝር ይሆን? ለዕረፍቱ ጊዜ ይቆየን ሌላው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በማር ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ጸሎት ይማረ። በረከቱም እጽፍ ድርብ ኹላ በዝታ ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ስላም ለፍልሰተ ሥጋከ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሀገረ ሢመትከ ቊስጥንጥንያ እምገዳመ ስደት ርሑቅ
መንፈስየ ሐድስ እግዚኦ ውስተ ከርሥየ ዕሩቅ
በዘይትዓቀብ ውስቴቱ ትምህርተ ዚአከ ጽድቅ
ከመ ውድየተ ወይን ሐዲስ በሐዲስ ዝቅ።

(❤❤
+ኦ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተብቊዕ ለነ ለውሉድከ ደቂቀ አዳም
+ሰሚዓነ ተግሣፀከ ከመ ንድኃን እምእሳቱ ዘኢይጠፍዕ ወዕጼሁ ዘኢይነውም
❤❤

❤❤አፈ ወርቅ አፈ መዐር ቅዱስ አባታችን ዮሐንስ ልሣነ ወርቅ ሆይ ድኩማን ልጆችህን በምልጃህ አስበን፣ ከማይጠፋው እሳትም ታሻግረን ዘንድ በጽኑዕ ቃልኪዳንህ ተማጽነንብሃል።❤❤)

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የቡሩክ_አብርሃም እና #የሚስቱ_ሐሪክ መታሰቢያቸው ነው። ዳግመኛም #የወጺፍ_ጻድቃን መታሰቢያቸው ነው። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለከ አብርሃም ቡሩክ
ወለብእሲትከ ሐሪክ
ዘፈረይክሙ ሕፃነ ቅዱስ አምላክ
ጺሑ ሊተ ፍኖተ ለበዊእ ኀበ ቦእክሙ ምስማክ
እስመ ፍኖትየ ተሐጽረ በሦክ።

ሰላም እብል ጻድቃነ አምዓተ
ገዳመ ወጺፍ ይዒሉ እለ መነኑ አብያተ
እስከ ረከብህ በኀሢሥ ዘአምላከ ያዕቆብ ቤተ
ኢወሀቡ ለመልታሕቶሙ እሙኀዘ አንብዕ ዕረፍተ
ወለዐይኖሙ ካዕበ ምንተኒ ኅድመተ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ለማስተማር የተጠራ #የአበ_ምኔቱ_የአባ_ሲኖዳ መታሰቢያው ነው። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለሲኖዳ እንተ አትሐተ ግብሮ
እንዘ አበ ምኔት ውእቱ ዘተጸውዐ ለምህሮ
አልባበ ድኩማን ያዕርፍ እምርሕቀተ ማይ እምተጽዕሮ
ቀዲሖ ሌሊተ ወፀዊሮ እንበለ መኑ ያእምሮ
ለለበዓቶሙ ይሜጡ አንቢሮ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር፣ ድርሳነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አፈ በረከት መምህረ ኲሉ ዓለም ወቅዱስ ሲኖዳ አበ ምኔት ወበእንተ ቡሩክ አብርሃም ወብእሲቱ ሐሪክ ወቅዱሳን ጻድቃን እለወጺፍ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

t.me @deaconmelakuyifru

#ጾማችንን_በማኅቶተ_ገዳም

#እንኳን_ለጾመ_ነቢያት_አደረሰን

"እንኪያስ እናምነው ዘንድ በቊዔት ያለ'ው የትኛው ነው? ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ኾነ እና ምንም ስለ ሰው ልጆች መዳን ባለ'ው አሳብ ምክንያት የሰብአዊ ባሕርያችንን ሥጋን ነሥቶ ቢወስድም ያ ቀድሞ በእግዚአብሔርነቱ በመለኮቱ የነበረው ባሕርዩ ኹሉ በምንም በምን መንገድ እንዳልተለወጠ፣ [መለኮት ከሰብአዊ ባሕርያችን ጋር በመዋሐዱም ሥጋን ከመለኮታዊ ባሕርዩ ሡቱፍ ያደርገው ዘንድ እንዲህ ማድረጉን] መመስከር ወይንስ አምላክን በአራዊት እና በከብቶች እንመስለው? ከዚህም በሚገኘው ነገር ምክንያት ሰው ራሱን ልክ እንደ አራዊት እና እንደ ምድር ተሳቢ እንስሳት ምሳሌ በማድረግ እነርሱን ያምልክን?"

#ማኅቶተ_ገዳም ገጽ 119 -120
(ቅዱስ እንጦንስ ሊፈትኑት ለመጡ የግሪክ ዕውቅ ፈላስፎች ከሰጠው መልስ)

"ጾምን ቸል አትበሏት፤ የክርስቶስን የሕይወት መንገድ የምትደነግግ (መሠረት) ናትና።"
                                                        
ጾሙን ለድኅነትና ለሰላም ለበጎ ዋጋ ኹሉ ያድርግልን።

t.me @deaconmelakuyifru

የኅዳር ፲፮ ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን #ለቅዱስ_አቡናፍር_ገዳማዊ እና #ለቅዱስ_አባ_ዳንኤል #ወቅዱስ_አባ_አኖሬዎስ (ጻድቅ ንጉሥ)፣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፮ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፮ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ቅዳሴሃ ለቤተ ክርስቲያን #ዘቅዱስ_ወቡሩክ_አቡናፈ_ገዳማዊ በአፍአ ሀገረ ምስር።

✍️፩-ኅዳር ፲፮ በዚህች ዕለት የከበረና የተመሰገነ #የገዳማዊ_አቡናፍር ከምስር ከተማ ውጭ የተሠራች ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው።

ለሰላም ለቅዳሴ ቤትከ በአፍአ ሀገር ዘምስር
እንተ ሐነፅዋ ኬነውት ወጠበብተ ምክር
አቡናፍር አቡየ ሠውረኒ አመ ዕለተ ፍዳ ወፃዕር
በዘከደነከ እምሐሩር ወቊር 
እምነ ርእስከ ወጽሕምከ ዘወረደ ጸጒር።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት የእስክንድርያ ሀገር አርባ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባት_አባ_ዮሐንስ አረፈ።

  + ይህ ቅዱስ የቆጵሮስ ሀገር ሰው ነው። እጅግ ባለጸጋ ነው። አባቱ አገረ ገዥ ነበርና ሚስትም አግብቶ ልጆችን ወለደ፣ ከዚህም በኋላ ሚስቱም ልጆቹም ሞቱ። ይህም ሲኾን ገንዘቡን ኹሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጠ፣ መጸወተ። እርሱም መንኲሶ በታላቅ ገድል የተጠመደ ሆኖ በጎ ሥራዎችን ትሩፋትን ጨምሮ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው።

  + በጎ ትሩፋቱን ገድሉንም በተመለከቱ ጊዜ ኤጲስ ቆጶሳት ደስ ተሰኙበትና ይዘው ያለፈቃዱ በግድ በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙትና በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ አስቀመጡት። የከበረ ወንጌልን አነበበ፣ በሹመቱና በክህነቱም ብርሃን ተገለጸ፣ ብዙዎች ድንቆች የሆኑ ተአምራትንም አደረገ። ለድኆችና ለችግረኞች ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የሚሹትን የሚሰጣቸው ሆነ ስለዚህም የሚራራ ዮሐንስ ( #ዮሐንስ_መሐሪ ) ተብሎ ተጠራ። በአይሁድና በአረማውያን ዘንድ የሚያስፈራ ሆነ፣ በመጽሐፈ ገድሉም እንደተጻፈ እጅግ ይፈሩትና ያከብሩት ነበርና መንጋዎቹንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው፣ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፣ በረከቱም እጽፍ ኹና በእኛ ትደርብን፣ ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም እብል ሊቀ ጳጳሳት ማሪ
ኃጢአተ ሕዝብ ዘይሰሪ
እንዘ ይዘሩ ንዋዮ በተሰፍዎ ዐስብ ደኃሪ
እስመ ኢፈቀደ ተረፈ ነዳያን ያጥሪ
ወበእንተዝ ተሰምየ ዮሐንስ መሐሪ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #ቅዱስ_ኪስጦስ በመኰንኑ እጅ በሰማዕትነት አረፈ።

ሰላም ለከ ሰማዕት ኪስጦስ
በእደ መኰንን መክሲሞስ
ቅሡፈ አባል በኲነኔ ወምቱረ ርእስ
ኀድፈኒ በጸሎትከ ውስተ ዛኅን ወመርስ
አመ ላዕሌየ ያመዓብል ባእስ።

✍️፬-ዳግመኛም በዚህች ዕለት በሮሜ አገር በመኰንን እስክንድሮስ እጅ #ቅድስት_ጣጡስ በሰማዕትነት አረፈች።

  + ይዘውም ወደ መኰንኑ ባቀረቧት ጊዜ ለአማልክት ሠዊ አላት፣ እርሷም ከፈጠረኝ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አልሠዋም ብላ መለሰች። መኰንኑም የፊቷን መሸፈኛ እንዲገልጡ አዘዘ፣ ውበቷ ሊነገር እጅግ የሚያስደንቅ ነበርና ንጉሡ ልቡ እስኪጠፋ ድረስ ኾነ። (እንዲህች ያሉትንና የነቅድስት አርሴማን፣ የነቅድስት አርዋን እና የሌሎቹንም ቅዱሳት ስነ ላህይ በምን ይናገሩታል? ድንቅ ነው!) ለእኅቶቻችን ደግሞ አንዱ ጣዖት የሚሆንባቸውና ከመንግሥተ እግዚአብሔር እየለየ ለክፋት ሠራዊት ግብር እንዲያድሩ የሚያደርጋቸው ነገር ሥነ ላህይ ነው። እንዲህች ያሉት ድንቅ ሰማዕታት ግን ይህንም እንኳ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ መሥዋዕት አድርገው በማቅረብ የቅድስና አክሊልን ይቀበሉበታል።

  + መኰንኑም ሥነ ላህይዋን እንደተመለከተ እባክሽ ይልቅስ ይህን ዕብደትሽን ትተሽ ለአማልክት ሠዊና ንግሥቴ ላድርግሽ አላት፣ 
ክብር ይግባውና እኔስ ከክርስቶስ መንጋዎች ወገን ነኝ፣ ከርሱም በቀር ለማንም አልሠዋም፣ ባይሆን የአማልክትህን ኃይላቸውን አይ ዘንድ ፍቀድልን አለችው። ፈቀደላትና ወስደው ከቤተ ጣዖቱ ቢያስገቧት ዐይኖቿን ቸሩ ጌታችን ኃይሉን እንዲገልጥ በመማጸን ወደላይ አነሳቻቸው። በኋላም በዚያ ጣዖት ያደረ ጋኔን መጮህ ጀመረ፣ ጣዖታቱም ኹሉ ወድቀው ተሰባበሩ፣ በዚያም አድሮ ሲያስት የቆየው ጋኔን ጣጡስ ሆይ እኔ ከአንቺ ምን አለኝ፣ ከደህና ማደሪያዬ አሳደድሽኝ፣ ንጉሡም ይህን አይቶ ተቆጣና አሥረው በግምባርዋ ደፍተው በበትሮች እንዲደበድቧት በአለንጋዎችም እንዲገርፏት አዘዘ። ከሥጋዋም በወተት አምሳል ነጭ ደም ፈሰሰ። ወደ እግዚአብሔርም በለመነች ጊዜ የሚደበድቧትን የእግዚአብሔር መላእክት ሲያሠቃዩዋቸው ተመለከተች፣ ቅድስት ጣጡስን ግን ሥቃያቸው የማይነካት ሆነ።

  + ኹለተኛም ለተራበ አንበሳ ሰጧት፣ አንበሳው ግን መጥቶ በክብር ከፊቷ ሰገደላትና የእግሮቿንም ትቢያ ላሰ። ከሰማይም እኔ፡ከአንቺ ጋር ነኝና ንጽሕት ጣጡስ ሆይ ደስ ይበልሽ የሚል ቃል መጣ። ንጉሡም ከክፉ ነገር የደረሰባት ምንም ምን እንደሌለ ተመልክቶ ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። በዚህችም ዕለት የሰማዕትነትን የድል አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች፣ በሌሊትም የሮሜ ጳጳስት መጥቶ በከበሩ ልብሶች ገነዛት፣ በወርቅና በብር ከተለበጠ የእብነ በረድ ሣጥን ውስጥም ጨመራትና በአማረ ቦታ በክብር አኖራት። ከሥጋዋም ቸሩ እግዚአብሔር ብዙ ድንቆችን ገለጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛም በዚህች ሰማዕት ጸሎት ይማረን፣ በረከቷም እጽፍ ኹና ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለጣጡስ ሥርጉተ አፍኣ ወውስጥ
በምግባር ፍጹም ውርበሃይማኖት ሥሉጥ
አመ ኮነት ሰማዕተ እንበለ ተምያጥ
አሕምሞ ሥጋሃ ኢክህሉ አስዋጥ
ወጸበለ እግራ ለሐሱ አናብስት መሠጥ።

✍️፭-ዳግመኛም በዚህች ዕለት የመነኰስ #አባ_ዳንኤል_ገዳማዊ እባ #የጻድቁ_ንጉሥ_አኖሬዎስ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው።

+ይህም አባ ዳንኤል የተባለው ጻድቅ፣ ታላቅ ገድለኛ ሲኾን እንጀራን ዓሣንም ቢሆን ማርንም ዘይትንም ቢሆን ከብቻው ቅጠል በቀር ሳይቀምስ አርባ ዓመት ተኩል በአስቄጥስ ገዳም ኖረ። ከብዙ ዘመንም በኋላ መነኰሳትን የሚፈትን የመመካት ጾር መጣበት። ይህ ፈተና አንድ ጊዜ ታላቁን ቅዱስ አባ መቃርስን በፈተነው ጊዜ ሰውን የሚወድ ቸሩ አምላካችን አባ መቃርስን ወደ ከተማ እንዲኼድና የወንድማማች ሚስቶችን ኹነው ልጆቻቸውን እያሳደጉ በከተማ ከሚኖሩት ኹለት ገድለኛ እናቶች እንዲማርና ጾሩ እንዲጠፋለት አድርጓል። አሁንም ይህ ታላቅ ቅዱስ አባ ዳንኤል የመጣበትን ጾር ቢመለከት መልአከ እግዚአብሔር ተገለጠና ወንድሜ፣ ቸሩ አምላካችን ክርስቶስ እንዲህ ያለውን የመመካት ከትሕትናና ከፍቅር በቀር አይወድምና ተው አለው። አባ ዳንኤልም ጌታዬ ይህን እንድተውና ጦሩም እንዲጠፋልኝ ከኔ የሚበልጥ ጻድቅ አሳየኝ አለው። መልአኩም በሮሜ የነገሠ ንጉሥ ኹኖ ሳለ ነገር ግን በገድሉ ጽኑዕ ታጋይ ተጋዳይ መነኰስ የሆነውን የጻድቁን አኖሬዎስን ነገር ነገረው። አባ ዳንኤልም ይህን ሲሰማ በምድር ላይ ተደፋና በራሱ ላይ አመድ ነስንሶ አለቀሰ
 በኃላም ይህን ገድለኛ ንጉሥ ሊያየው ወደደና ጸለየ።

  + ብርህት ደመናም መጣችለትና ተጭኖ ወደ ሮሜው ንጉሥ ዘንድ ኼደ። እንደደረሰም አገልጋዩን ጠርቶ እባክህ ወንድሜ ንጉሡን ማግኘት እሻለሁና የሚያገናኘኝን መኰንን አገናኘኝ አለው። እርሱም እኔ ባስገባህስ አትገባምን? አለው። እግዚአብሔር ይባርክህ ልጄ አስገባኝ አለው። አባቴ ሆይ ግን ምድራዊ የሆነ ሟች ፈራሽ ንጉሥን ስለምን ማየትን ወደድህ አለው፣ እርሱም ቸሩ ጌታዬ ስላዘዘኝ እ

ንጂ ነው አለው። በኋላም ቆየን ለጌታዬ የሚሻውን ገዝቼ ልምጣ ብሎ ወጣና ጥቂት ጨው አምባሻና እና መጻጻ ገዝቶ መጣ። ይህንም ይዞ አብማሻ ጨው መጻጻና የጎመን ቅጠልም ገዝቶ ወደ ጌታው ወደ ንጉሡ እና ወደ ንጉሡ መምህር አባ አውሎጊስ ዘንድ ገባ፣ አባ ዳንኤልንም በውጭ ተወው። ንጉሡም ረዳቱን አንተ አላዋቂ ነህን? ስለምን አባ ዳንኤልን በአፍአ ተውኸው አለውና ከመምህሩ ከአውሎጊስ ጋራ ወጣ። ለአባ ዳንኤልም ሰገዱለት። ሰላምታም ተሰጣጥተው ወደ ቤተ መንግሥት አስገቡትና በአንድነት ተቀመጡ።

  + ዘጠኝ ሰዓትም በሆነ ጊዜ ለማዕድ ሲሰየሙ አባ ዳንኤል እንዳይታመም ፈርቶ ጌቶቼ እንጀራን ባለመብላቴ በእኔ ላይ አታጒረምርሙ፣ እንዳልታመም ፈርቼ ነው አላቸው። ጸሎትንም ጸለዩ፣ ከዚህም በኋላ ንጉሥ አኖሬዎስ አባ ዳንኤልን ስለአመጣጡ መረመረው፣ አባ ዳንኤልም የሚቻልህስ ከሆነ ከንጉሡ ዘንድ አስገባኝ፣ በጌታ ክርስቶስ ትእዛዝ መጥቻለህይና አለው፣ ነገ አስገባሃለሁ አለው። በማግስቱም አኖሬዎስ ዐይን የሚበዘብዝ ልብሰ መንግሥቱን ለብሶ በዙፋኑ ላይ ተቀመጠ፣ አባ ዳንኤልንም አስገቡት በአየውም ጊዜ ፈርቶ ተንቀጠቀጠ፣ ረዳቱም መፍራቱን አይቶ ወደ ማደሪያው መለሰው። ንጉሡም ችሎቱን ሲጨርስ ልብሰ መንግሥቱን ጨርሶ ልብሰ ምንኲስናውን ለብሶ ወደ አባ ዳንኤል መጣ፣ እርሱም ወንድሜ ሆይ በልቤ ያለውን ነግሬው ወደ ቦታዬ እመለስ ዘንድ ወደ ንጉሡ ለምን አላስገባኸኝም አለው። አኖሬዎስም አባቴ ሆይ አልገ አልገባህምን? ለዚህች ምድር ንጉሥ ብለው የሰየሙኝ እኔ ነኝ አለው፣ አባ ዳንኤልን በሰማ ጊዜ ከእግሩ በታች ሰገደለትና አኗኗሩን ሁሉ ይነግረ ዘንድ በጌታችን ስም አማጸነው። አኖሬዎስም በጅግ ሥራው ፈክሞ ከሚያገኘው በቀር (ይህም ሰሌን መታታት ነው) ሳይበላ ሳይለብስ አርባ ዓመታት እንደሆነው፣ የሚተርፈውንም ለድኆች እንደሚሸጥ ምግቡም እንጀራና ጨው ቅጠል መጻጻም እንደሆነ፣ የማንንም ገንዘብ ለመቀማት እንዳልደፈረ ድንግልናውንም መጠበቁን ነገረው። 

  + አባ ዳንኤልም ከእግሩ በታች ሰገደለትና አባቴ በአንተ ላይ ስለተመካሁ ይቅር በለኝ አለው። ከዚህም በኋላ አባ ዳንኤል ፈጽሞ እያዘነ ወደ ቦታው ተመለሰ። ከኹለት ወራትም በኋላ ጻድቁ ንጉሥ አኖሬዎስ ከመምህሩ ተማክሮ መንግስቱን ጥሎ ወደ አባ ዳንኤል ኼደ። መልአከ እግዚአብሔርም ተሸክሚ አደረሰው። እነርሱም በአንድነት ሲጋደሉ በፍቅር ኑረው በዚህች ቅድስት እለት በአንድነት አረፉ። እንዲሁም መምህሩ አውሎጊስና ረዳቱ በዚያች ዕለት በአንድነት አረፉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በቅድስት ጸሎቱ ይማረን፣ በረከቱም እጽፍ ኹና በኹላችን ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ስውላም ለአኖሬዎስ እንዘ ባዕል ዘአትጸነሰ
ወለዳንኤል ሱታፉ አስኬማ መላእክት ዘለብሰ
እንበይነ አንጽሑ ሥጋ ወእንበይነ ቀደሱ ነፍሰ
እምበዓት መነኰሰ ወእምነ መንበር ንጉሠ
እግዚአብሔር ዮም ኅቡረ አፍለሰ።

ሰላም ለአውሎጊስ ለአኖሬዎስ መምህሩ
ወሰላም ለረድኡ ዘሠናይ ዝክሩ
በዋሕድ ልብ እንዘ ይትፋቀሩ
በውስተ ዓለም ከመ አሐተኔ ነበሩ
በመንግሥተ ሰማይ ዮም ኅቡረ ኀደሩ።

✍️፮-ዳግመኛም በዚህች ዕለት በሐይቅ ዳር እንዳለ ጽጌረዳ መዐዛው የሚጥም #የፊቅጦር መታሰቢያው ነው። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለከ ነቃዌ መጻሕፍት ማዕነቅ
ለማርያም ድንግል በርእሰ ደብተራ ምጡቅ
ፊቅጦር ምዑዝ እምጽጌ ረዳ ዘሐይቅ
አእሩግ ተፈሥሑ በትምህርተ ዚአከ ጽድቅ
ወበተግሣጽከ ተሐሥዩ ደቂቅ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ አቡናፍር ጻድቅ ገዳማዊ ወበእንተ ቅዱስ ዳንኤል ገዳማዊ ወአኖሬዎስ ጻድቅ ንጉሠ ሮሜ ወበእንተ ቅድስት ጣጡስ ሰማዕት ወቅዱስ ፊቅጦር ምዑዝ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

የኅዳር ፲፭ ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን #ለማር_ቅዱስ_ሚናስ_ሰማዕት እና #ለሊቀ_ጳጳሳት_ቅዱስ_ሚናስ_ዳግማዊ፣ #ለቅዱስ_ቂርቆስ_ወቅድስት_ኢየሉጣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፭ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፭ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮነ ሰማዕተ #ቅዱስ_ሚናስ ዘትርጓሜ ስሙ ምእመን ወቡሩክ።

✍️፩-ኅዳር ፲፭ በዚህች ዕለት የስሙ ትርጓሜ ቡሩክና የታመነ የኾነ #ቅዱስ_ሚናስ በሰማዕትነት አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ አባቱ አባቅዮስ ከሚባል አገር ሲሆን ስሙም አውዶክስዮስ ነው። እርሱም አገረ ገዥነት ተሹሞ ሳለ ወንድሙ ተመቅኝቶት በንጉሥ ዘንድ ነገር ሠራበት፣ ንጉሡም ከዚህ አንስቶ ወደ አፍራቅያ አገር ሰደደውና በዚያም አገረ ገዥ አድርጎ ሾመው። እርሱም ደግና ለሰው አዛኝ፣ ለድኃ የሚራራ፣ የዋህ ነውና የአገር ሰዎች ኹሉ እጅጉን ይወዱት ነበር። እናቱም ልጅ ስላልነበራት በዚህ ታዝን ነበር። አንድ ዕለት ወደ እመቤታችን ቤተ ክርስቲያን በእመቤታችን በዓል ቀን ስትኼድ የክርስቲያንን ወገኖች ያማሩ ልብሶች ለብሰው ከልጆቻቸው ጋራ ደስ እያላቸው ሲገቡበየቻቸው። በእመቤታችንም ሥዕለ አድኅኖ ፊት እያለቀሰች ጽኑዕ ተማጽኖን ተማጸነች። ቡሩክ የሆነ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ልጅ እንድትሰጣት ተማጸነች። ከሥዕሏም አሜን የሚል ድምጽ ሰማች። 

  + በኋላም ወደቤቷ ገብታ ለባሏ ይህን ነገር ነገረቸው፣ እርሱም የእግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁን አለ። ከጥቂት ቀና በኋላ ይህ ደገ'ኛ መስተጋድል ሰማዕት ቅዱስ ሚናስ ተጸነሰ። ስሙንም ደግሞ ከሥዕለ ማርያም እንደሰማችው ስያሜ ሚናስ ብለው ጠሩት። ጥቂትም በአደገ ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት። ዐሥራ ኹለት ኢኣነትም ሲሆነው፣ በመልካም ሽምግልና ኹኖ አባቱ አረፈ። ከርሱም በኋላ በሦስተኛው ዓመት እናቱ አረፈች። ቅዱስ ሚናስ ሰማዕቱም ብቻውን ቀረ።

  + መኳንንቱም አባቱን አብዝተው ከመውደዳቸው የተነሳ ቅዱስ ሚናስን በአባቱ ፈንታ ምስፍናን ሾሙት፣ እርሱም አምልኮተ እግዚአብሔርን እንዳጸና ቆየ። ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም ቸሩን የክብር ባለቤት ክርስቶስን በካደውና ሰዎች ጣዖታትን እንዲያመልኩ ጊዜ ብዙዎች ስለቸሩ ክርስቶስ ፍቅር ሰማዕት ኾኑ። ቅዱስ ሚናስም ይህን ሲሰማ ሹመቱን ትቶ ወደ ገዳም ገብቶ በታላቅ ተጋድሎ እየተጋደለ ለብዙ ዘመናት ኖረ። በአንዲቱም ዕለት ሰማያት ተከፍተውለት ለቅዱሳን ሰማዕታት የሚሰጣቸውን የብርሃን አክሊላት ሲያቀዳጇቸው ተመለከተ፣ እንዲሁም ስለክርስቶስ ስም በመከራ የደከመ ይህን አክሊል ይቀበላል የሚል ቃልን ሰማ። በዚያንም ጊዜ ወደ ከተማ ተመለሰና ክብር ይግባውና በክርስቶስ ስም ታመነ፣ እርሱም ከከበሩ ሰዎች ወገን ነበርና ኹላቸውም አብዝተው ለመኑት አባበሉት፣ መኰንኑም ብዙ ቃልኪዳን እየገባ ሊያባብለው ቢሞክር አልኾነለትም፣ ኋላም ባልሆነለት ጊዜ ጽኑዕ ሥቃያትን አሠቃየው፣ ቅዱስ ሚናስ ግን ልቡ ለቸሩ የክብር ባለቤት አምላካችን ጨክኖ ስለፍቅሩ ለመሞት መጥቷልና ልቡ ፈጽሞ አልተናወጸበትም። መኰንኑም ማሠቃየትን በሰለቸ ጊዜ ቅድስት ራሱን በሰይፍ ከሰውነቱ ይለዩዋት ዘንድ አዘዘ። ቅዱሱም የሰማዕትነትን አክሊል በመንግስተ ሰማያት ተቀበለ። (ቅዱሱ ሦስት አክሊላትን የተቀዳጀ ድንቅ መስተጋድል ሰማዕት ነው።) እርሱንም ተመልክተው ብዙዎች በቸሩ አምላካችን አምነው ሰማዕት ኾኑ። ከዚያም የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ይዘው በእሳት እብዲያቃጥሉት መኰንኑ አዘዘና ሊያቃጥሉት ቢሉ አልኾነላቸውም። ምእመናንም ወስደው ዘመነ መከራው እስኪፈጸም በአማረ ቦታ አኖሩት። 

  + ዘመነ ሰማዕታትም ካለፈ በኋላ የመርዩጥ አገር ሰዎች ከአምስቱ አገሮች ሠራዊትን ሊያከማቹ ወደዱ። የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ረዳት ይኾናቸው ዘንድ ከእርሳቸው ጋር ወሰዱት። በባሕርም ላይ በመርከብ እየኼዱ ሳሉ አንገታቸው እንደገመል ፊታቸው ደግሞ እንደከይሲ ያሉ አራዊት የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ሊልሱ አንገታቸውን ሲያስረዝሙ ከቅዱስ ሚናስ ሥጋ እሳት ወጥታ በላቻቸው። ይህንም ተአምራት ያዩት ኹሉ በቅዱሳኑ ላይ ድንቅን የሚያደርገውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ። 

  + ወደ እስክንድርያም ሊኼዱ ወደው የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ወደዚያ ሊወስዱ በገመል ጭነው ቢሉ ገመሉ አልንቀሳቀስም አለ፣ በሌላም ገመል ቢሉ አልኾነም። በመጨረሻም እግዚአብሔር የወደደው ቦታ መኾኑን አውቀው በዚያ በክብር ቀበሩት። ለብዙ ዘመናትም በዝዝያ ከኖረ በኋላ ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር አምላካችን የአንድ እረኛ ምክንያት በበጎቹ ገለጠው። የዚህም ዜና በሰኔ ዐሥራ አምስት ቀን ይተረካል፣ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በታላቁ ሰማዕት ማር ቅዱስ ሚናስ ጸሎት ይማረን፣ በረከቱም እጽፍ ኹና ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለከ ሐራዊ መስፍን
ሰማዕተ መድኅን
ዘሰመየተከ ሚናስ ዘፆረተከ ማሕፀን
አመ ጸለየት ጸሎተ እንዘ ይእቲ መካ'ን
እምሥዕለ ማርያም ሰሚዓ ዘይቤ አሜን።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት የእስክንድርያ ስሳ አንደኛው ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባ_ሚናስ_ዳግማዊ አረፈ።

  + ይህ ቅዱስ በታናሽነቱ ያለፍላጎቱ ወላጆቹ ሚስት አጋቡት። እርሱም የወላጆቹን ትእዛዝ ላለመተላለፍና እነርሱንም ላለማሳዘን ሥርዓቱን ኹሉ በቤተ ክርስቲያን ፈጸሙ። ይህ ኹሉ ግን ለርሱ ልክ እንደሕልም እንጂ እውነት እንደኾነ አያስብም ነበር። በኋላም ወደ ሙሽሪቷ አዳራሽ ሲገባ ትክ ብሎ ተመለከታትና እኅቴ ሰው ዓለሙን ኹሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ቢያጠፋ ምን ይጠቅመዋል። እንግዲህ ንጽሕናችንን ለመጠበቅ ቃል ኪዳን እንድርግ አላትና ቃል ተገባቡ። በኋላም በዚያው ትቷት ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገባና በአባ መቃርስ ገዳም ውስት በዚያ መንኲሶ በገድል ተጸምዶ መኖር ጀመረ። ከርሱ በፊት የነበረው ሊቀ ጳጳሳት ሲያርፍም ያለውዴታው በግድ ሊቀ ጳጳዳት አድርገው ሾሙትና በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ተቀመጠ።

  + እርሱም መንጋዎቹን በቅን ፍርድ እየጠበቃቸውና እያስተማራቸው ዐሥራ ስምንት ዓመት ኑሮ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ በረከቱም እጽፍ ድርብ ኹና ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም እብል ለሚናስ ዳግም
እንተ ለብሰ ፃማ በውስተ ገዳም
ወመነነ ኲሎ ፍትወተ ሥጋ ወደም
ረስዮ ከመ ጽላሎት ሀልዎተ ዝንቱ ዓለም
ወከመ ጽሙዕ ዘይሰቲ በሕልም።

ሰላም እብል ዘጳኲምዮስ ቤተ
ዘጸገወቶ ማርያም አዕባነ ብርሃን ክልኤተ
በዛቲ ዕለት ከመ አድምዐ መባሕተ
ጢሞቴዎስ አብ ቀደሰ ክሡተ
ወኢየሱስ ክርስቶስ አተበ መሥዋዕተ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የቅዱስ_ቂርቆስ_ሰማዕት ልደቱ ነው።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ ማር ሚናስ ሰማዕት ወቅዱስ ሚናስ (ዳግማዊ) ሊቀ ጳጳሳት ወቅዱስ ቂርቆስ ሰማዕት ወእሙ ቅድስት ኢየሉጣ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

የኅዳር ፲፬ ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን #ለቅዱስ_መርትያኖስ_ኤጲስ_ቆጶስ እና #ለቅዱስ_ዮሐንስ_ጻድቅ_ዘደብረ_ቢዘን፣ #ለቅዱስ_ጻድቅ_ዳንኤል_ገዳማዊ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፬ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ አዕረፈ አብ #ቅዱስ_አባ_መርትያኖስ ኤጲስ ቆጶስ ዘሀገረ ጠራክያ።

✍️፩-ኅዳር ፲፬ በዚህች ዕለት የጠራክያ አገር ኤጲስ ቆጶስ #ቅዱስ_አባ_መርትያኖስ አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ ሶርያ በምትባል አገር የተወለደ ሲኾን ወላጆቹም ክርስቲያን ናቸው። እርሱም በገድል የተጠመደ ተጋዳይ ነው። አርዮሳውያንንም በክህደታቸው ምክንያት የሚያወግዛቸውና የሚያሳድዳቸው ኾነ። እነርሱም እነርሱም በርሱ ላይ ልዩ ልዩ መከራ ያደርሱበትና በሚያልፍበትም ጎዳና ጠብቀው ይዘውም ሜዳ ላይ እየጎተቱ ያሠቃዩት ይደበድቡትም ነበር። እነርሱም አሳደዱትና ተሰዶ ሸሽቶ ወደ ኤርትራ ባሕር ዳር መጥቶ በዚያ ከምድር የሚበቅሉትን ቅጠሎች እየተመገበ በዋሻ ተወስኖ ለብዙ ዓመታት ኖረ። 

  + ቸሩ እግዚብሔርም ለኤጲስ ቆጶስነት መረጠውና ይህ ጽኑዕ ተጋድሎው በአገሩ ሲሰማ ይዘው ወሰዱና ጠራክያ በምትባል አገር ላይ ኤጲስ ቆጶስነት ሾሙት። እርሱም እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኘው በጎ ምግባር ተጓዘ። በርሱም የኤጲስ ቆጶስነት ዘመን በብዙዎች ላይ ሰላም ፍቅር አንድነትም ኾነ። ቸሩ እግዚአብሔርም በዚህ ቅዱስ አባት እጆች ብዙ ድንቆች ተአምራትን አድርጓል። ከነዚህም አንዱ ሰዎች ውንድ ሰው ሙቶባቸው ይዘው ሊቀብሩ ሲኼዱ አንድ ክፉ ሰው ከመንገድ ቆይቶ ዕዳ አለበትና አትወስዱትም አላቸው። ቅዱሱ አባታችን ብዙ ቢለምነውም ሊሰማ አልቻለም። በመጨረሻም አባ መርትያኖስ ወደ ሰማይ ዐይኖቹን አቅንቶ ቢጸልይ ያ የሞተ ሰው አፈፍ ብሎ ተነሳና ምንም ምን ዕዳ እንደሌለበት መሰከረ። አባ መርትያኖስም ልጄ ስለምን በሐሰት ተናገርህ? ኹሉም የሚመረምረውን ቸሩን እግዚአብሔርን አትፈራውምን አለው። ከዚያም ያ ዓመፀኛ ሰው ሞተና ያ ሙቶ ሊቀ'በር የነበረው ሰው ግን ከሞት ተነስዮ በሰላም ወደቤቱ ኼደ። ከዚህም በኋላ ቅዱስ መርትያኖስ ብዙ ዘመናትን ኖረ፣ መልካም፡አገልግሎቱንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በቅዱስ መርትያኖስ ጸሎት ይማረን፣ በረከቱም በእኛ ላይ እጽፍ ኹና ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለመርትያኖስ ምሉአ ጸጋ ወሀብት
ከመ ይስብክ ሃይማኖተ በመጣርያ እንተ ተውህበቶ ሢመት
እመርዮሳውያን ሕዝብ ሶበ ረከቦ ስደት
ኀበ ሖረ ወፈለሰ ውስተ ምድር ርኅቅት
በኃይለ ጸሎቱ ተንሥአ ምውት።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ለፋርስ ንጉሥ ተአምራትን ያደረገና ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያዳመነው #የአባ_ዳንኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

  + ይህም የኾነው እንዲህ ነው። የፋርስይ ንጉሥ በጽኑዕ የሆድ በሽታ ይያዝና ብዙ ባለ መድኃኒቶች ጋር ቢደክማ ቢታገልም አልሆነለትም። ንጉሡም ከማዕዱ ከፍሎ የሚያበላው አንድ ሥራይኛ ነበረው። ያንንም ሥራይና እኔ ከምበላው አብልቼ ከምጠጣው አጠጥቼ የማኖርህ እንዲህ ካለው ችግር የማታድነኝ ከኾነማ ምን ሊበጀኝ አለው። ያም ሥራይኛ በተንኮል ንጉሡን እንዲህ አለው። አንድ ልጅ ብቻ ያላቸውን ሰዎች በገንዘብ ልጃቸውን ግዛቸውና አምጥተህ እናቱ አጥብቃ ትሠረው፣ አባቱም ይረደውና በሱ ደም ትድናለሁ አለው። ይህንም ማለቱ ንጉሥ ነውና ፈርቶ ምንም አያደርግም ብሎ ነው፣ ነገር ግን ንጉሡ ለወታደሮቹ ገንዘብ ሰጥቶ እንዲፈልጉ ላካቸው፣ ኋላም አንድ ባልና ሚስት ድኆች የኾኑ አገኙና አመጧቸው። እኒያም ድኆች ባልና ሚስት በፍቅረ ንዋይ ታለሉና ለልጃቸው ምንም ሳይሳሱ እናቱ አጥብቃ አሥራ ያዘችው። አባቱም ሊያርደው ሾተሉን አነሳ። ሕጻኑም ማንም የሚያድነውን ባጣ ጊዜ ዐይኖቹን ወደላይ አቅንቶ እግዚአብሔር እንዲያድነው ይማጸን ጀመረ። አምላካችንም የንጉሡን ልብ አራራለትና ፈትታችሁ ልቀቁት አለና ለቀቀው። አስቀርቦም ምን እያልህ ነበር የምትጸልየው አለው። እርሱም እናትና አባቴም ኹሉም የሚያድነኝን ባጣ ዐይኖቼን አቅንቼ ሰማያዊውን አምላኬን እንዲያድነኝ ነው የተማጸንሁት አለው። 

  + ቸሩ አምላካችንም ለዚህ የንጉሡ ውለታ ወደ በጎ መንገድ ሊመልሰው ወደደና ታላቁን መነኰስ ቅዱስ አባ ዳንኤልን ወደ ንጉሡ ሰደደው። አባ ዳንኤልም መጥቶ በንጉሡ ፊት ድንቅ የኾኑ ተአምራትን አደረገ፣ ንጉሡንም ፈወሰውና የቀናቸውን የእውነት መንገድ አስተማረውና በክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ አሳመነውና አጠመቀው። ከዚህም በኋላ ወደ በዓቱ ተመልሲ እየተጋደለ ኖረ፣ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በአባ ዳንኤል ጸሎይ ይማረን፣ በረከቱም በዝታ ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም እብል ለዳንኤል መነኰስ
እንተ ወሀቦ ፈውሰ ለንጉሠ ፋርስ
ድኅረ እመጥባሕት ቤዘዎ በተራኅርኆ መንፈስ
እምነ እሙ ነዳዪት ወእመቡሁ ጽኑስ
ለዘትሠየጦ በወርቅ ለሕፃን ንኡስ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  #የሱራስጦስ #የእንድራዎስ #የመብሪኖስ #የራጢና እንዲሁም ደግሞ #የጋርሴስ #የበጥላን እና የደብረ ቢዘኑም የሃይማኖት መምህር #የአባ_ዮሐንስ መታሰቢያቸው ነው። በደብረ ቀልሞን የተሠራችም ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው፣ በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለዮሐንስ ገሣጼ ሕዝብ አብዳን
በከሊአ ዝናም ወጠል መጠነ ሠልስቱ አዝማን
እንበይነ ዝንቱ ኃይልከ ኃይለ አጥናን
ትትሜሰል በኤልያስ ወበዮሐንስ ካህን
ወበቴስባን ትትሜሰል ቢዘን።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ መርትያኖስ ኤጲስ ቆጶስ ወቅዱስ ዳንኤል ገዳማዊ መስተጋድል ወቅዱስ ዮሐንስ መምህር ዘደብረ ቢዘን ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

t.me @deaconmelakuyifru

የኅዳር ፲፫ ዝክረ ቅዱሳን

እንኳን #ለቅዱሳን_አእላፍ_መላእክት እና #ለቅዱስ_ተስከናፍር_መኰንነ_ሮሜ፣ #ለቅዱስ_ዘካርያስ_ሊቀ_ጳጳሳት ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፫ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፫ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ አዘዙነ መምህራነ ቤተ ክርስቲያን ከመ ንግበር ተዝካረ በዓሎሙ #ለአእላፍ_ቅዱሳን_መላእክት።

✍️፩-ኅዳር ፲፫ በዚህች ዕለት #የአእላፍ_ቅዱሳን_መላእክትን የበዓላቸውን መታሰቢያ እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አዘዙን።

  + ውድ የሥላሴ ልጆች፣ የሥላሴን የቸርነቱን ፏፏቴ የምሕረቱንም ውቂያኖስ ለማየት እና በዚያም ሰጥሞ በፍቅር ለመቅረት የምንሻስ ከሆን ፍጡራንን ለምን ፈጠረ ብለን እንጠይቅ። መልሱን ስንፈልግ ቸርነቱ ጋር እንደርሳለንና። ሥላሴ ፍጡራንን ሊፈጥር የሳበው ፍቅሩ እና ቸርነቱ እንጂ ምንም ምን ሌላ አይደለምና።

+ መላእክት የምንላቸው ከሀያ ሁለቱ ሠናያን ፍጡራነ እግዚአብሔር መኻከል አንደኞቹ ናቸው። ቅዱስ ኤጲፋንዮስ ሊቁ በመጽሐፈ አክሲማሮስ እንደሚነግረን፣ ሥላሴ ቅድመ ዓለም በባህርዩ ምስጉን ሁኖ ሲኖር ክብሩ በርሱ ብቻ እንደቀረ ዐይቶ ፍጡራንን ይፈጥር ዘንድ አሰበ። አስቦም አልቀረ በሦስተ መንገድ እና በስድስት እለታት ሀያ ሁለት ወገን አድርጎ ቁጥር የማይገኝላቸውን ፍጡራን ፈጠረ።
      የፈጠረባቸውም ሦስት መንገዶች እሊህ ናቸው፥
  1/ በሀልዮ (በማሰብ)፥ በዚህ መንገድ የፈጠረው ሰባት ፍጥረት ሲሆን ይህን መንገድ የፈጠረበት ሰማዕያን የሆኑት ፍጡራን መላእክት እስኪገኙ ድረስ ነበር።
  2/ በነቢብ (በመናገር)፥ ይህን መንገድ ደግሞ አሥራ አራት ፍጡራንን ፍርጥሮበታል። ይኸውም ከላይ ባለ'ው መንገድ ሰማዕያን ለባውያን የሆኑ ፍጡራን (መላእክት) ተገኝተዋልና በነቢብ መፍጠር ጀመረ።
  3/ በገቢር (በመሥራት)፥ በዚህ መንገድ የተፈጠረው ልዩው ፍጡር አንድ ፍጡር ብቻ ነው። 

በእሊህ ሦስት መንገዶች ከተፈጡሩት ፍጡራን ወገን ለባውያን (reasonable beings) የሆኑት እና ሥላሴን አመስግነው ከክብረ ሥላሴ ለመውረስ የተፈጠሩት ሁለት ፍጡራን ብቻ ናቸው። እነርሱም መላእክት እና የሥላሴ አርአያ የተሰጠው የሰው ልጅ ናቸው። የሰው ልጅን ጉዳይ ከዚህ አቆይተን ስለመላእክት እንነጋገር።

¶ መልአክ፥  በግእዙ "ለአከ- ላከ" ካለው ግሥ የተገኘ ሲሆን መልእክተኛ ማለት ነው። ይኸውም የፍጡራንን (የሰው ልጆችን ልመና) ቅድመ መንበረ ሥላሴ የሚያሳርጉ፣ የሥላሴን የምሕረትና የቸርነት ስጦታ ወደ ፍጡራን የሚያደርሱ ናቸው። 

መላእክት የተፈጠሩት በእለተ እሑድ ሲሆን የተፈጠሩትም ከእሳትና ከነፋስ ነው። ይህም ሲባል አክሲማሮስ እንደሚነገረን ግብራቸውን ማለትም እንደእሳት ረቂቅ እንደነፋስ ፈጣን ለማለት እንጂ ከባህርየ ሥጋ ተፈጥረውስ ቢሆን መፍረስ መበስበስ ባገኛቸው ነበር። ቄርሎስ ዘኢትዮጵያ የተባለው ሊቅ "ዘይሬስዮሙ ለመላእክቲሁ #መንፈሰ ወለእለ ይትለአክዎ #ነደ እሳት- መላእክቱን #መንፈስ (እምደነፋስ ቀሊላን ረቂቃን) የሚላኩትንም #የእሳት ነበልባል የሚያደርጋቸው " እንዳለው በሰአታቱ። ስለዚህም እም ኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደ መኖር) አምጥቶ ፈጥሯቸዋል። ሲፈጥራቸው አስቀድሞ መኖሪያቸው ሰማያትን አዘጋጅቶ ነው። ስለዚህ ጉዳይ ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ እንደሚለን ሥላሴ ሰማያትን አስቀድሞ መፍጠሩ፥
    ሀ/ መላእክትን አስቀድሞ ፈጥሮ ቢሆን "እርሱ ሲመሠረት እኛ ሌላውን ሠራን፥ እሱ ሲመሠረት አብረን መሠረትን" ባሉ ነበርና ይህችን ድኩም ሕሊና ከመላእክት ለማጥፋት ቀድሞ ሰማያትን ፈጠረ። ይኸውም ይታወቅ ዘንድ አቡሃ ለሐሰት የተባለ እኩይ ዲያብሎስ ከሰማያት በኋላ ተፈጥሮም እንኳን "እኔ ፈጣሪ ነኝ" ብሏልና።
   ለ/ ዳግመኛም ዛሬ አንድ እንግዳ የሚጠራ ሰው ለእንግዳው የሚሆነውን ማደሪያ ሳያዘጋጅ እንዳይጠራው፣ እንዲሁ ሁሉ ሥላሴም የመላእክትን ማደሪያቸውን መኖሪያቸውን አዘጋጅቶ መላእክቱን መፍጠሩ እንዴት የተገባ እንደሆነ ልብ እንበል። 

+ #መላእክት ተፈጥሯቸው እንዲህ ሁኖ ሲፈጠሩ፥ በአጠቃላይ መቶ ነገደ መላእክት እና አሥር ሊቃነ መላእክት ሁነው ነበር። እሊህንም ሦስቱን ሰማያት #ኢዮር፣ #ራማ እና #ኤረርን ከአሥር ከተማ አድርጎ ከፍሎ በዚያ አስቀምጧቸዋል። 

+ አሥር አሥሩን ነገደ መላእክት አንድ አንድ አለቃ እየሾመ በየከተማው አኑሯቸዋል። የነገደ መላእክቱ ስምም ከላይ ወደ ታች ይህ ነው።

  ° አጋእዝት፥ አለቃቸው ሳጥናኤል(ነበረ)
  ° ኪሩቤል፥ አለቃቸው ኪሩብ ሲሆን በዐይን የተሸለሙ የካህናት አምሳል የሆኑ ነገደ መላእክት ናቸው።
  ° ሱራፌል፥ አለቃቸው ሱራፊ ሲባል ስድስት አክናፍ እና ስድስ እጆች ያሏቸው ነገደ መላእክት እሊህ ናቸው።
  ° ኃይላት፥ አለቃቸው #መልአከ ኃይል #መልአከ ምክር #መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል ነው። ሰይፍን የሚይዙ ሊቃነ መላእክት እሊህ ናቸው። እሊህን አራቱን ሊቃነ፡መላእክት እና አርባውን ነገድ በኢዮር ሰማይ ላይ ኢዮርን አራት ከተማ አድርጎ ከላይ ወደታች አኖራቸው።

  ° አርባብ፥ አለቃቸው መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብኤል ሲሆን የሥላሴ አጋፋሪ፣ እልፍኝ አስከልካዮች ይላቸዋል አክሲማሮስ።
  °መናብርት፥ የእነዚህ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ሲሆን አክሲማሮስ እንደሚነግረን ሀያ አራቱን ካህናተ ሰማይ የተመረጡት ከእነዚህ ነገደ መላእክት ነው።
  ° ስልጣናት፥ አለቃቸው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሱርያል ሲሆን እሊህን የሥላሴ ነጋሪት መችዎች ለስባሔ የሚያነቁ ይላቸዋል። እሊህን ሦስቱን ሊቃነ መላእክት እና ሠላሳውን ነገደ መላእክት በራማ ሰማይ ላይ ራማን ከሦስት ከተማ አድርጎ ከፍሎ በዚያ አኑሯቸዋል።

  ° መኳንንት፥ እሊህ ደግሞ አለቃቸው መልአኩ ሰዳክያል (ሰዳካኤል) ይባላል። 
  ° ሊቃናት፥ አለቃቸው መልአኩ ሰላትያል (ሰላታኤል) ይባላል።
  ° መላእክት፥ አለቃቸው መልአኩ አናንያል (አናንኤል) ይባላል። እዚህ ጋር "መላእክት" ብለን የተናገርነው የነገዱ ስም መሆኑን ልብ ይሏል።

+ እኒህ ረቂቃን ፍጡራን የተለያየ ዓይነት፣ የተለያየ ተፈጥሮ አላቸው። ይኸውም ማለት በክንፋቸው ሀገራትን አኅጉራትን የሚሸፍኑ፣ ቁመታቸው ከጠፈር እስከ በርባሮስ (መሠረተ ምድር) ድረስ የሚደርሱም አሉ። ልዩ ልዩ ዓይነት ናቸው። 
+ ሌላኛው ነገር፣ መላእክት ለተልእኮ ካልሆነ በቀር ሥላሴ ካስቀመጣቸው ቦታ በፍጹም አይወጡም። በዚህም ተልእኳቸው ምክንያት በተለያየ ጊዜ ወደ ሰው ልጆች ተልከው በሠሩት ስራ የሚዘከሩ መላእክት አሉ። ለምሳሌም ያህል ብናነሳ ወደ ታላቁ የእግዚአብሔር አፍ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ እንሂድ፥
  - መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወደ ጦቢትና ቤተሰቦቹ ተልኮ እንደነበረ እና ስላደረገላቸው ድንቆች በመጽሐፈ ጦቢት እንመለከታለን
  - መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በተለያየ ጊዜ እስራኤልን ሲመራቸው፣ ወደ ዳንኤል ሲላክ፣ ወደ ጌድዮን ወደ ሌሎቹም ሲላክ እናነባለን።
 - መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ሠለስቱ ደቂቅን ለማዳን፣ ዘካርያስን ለማብሠር፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ የሰው ልጆች ስንናፍቀው የነበረውን ደስታ ለማብሠር ወደ አዛኝቷ የማሂት ርግብ ተልኮ ሲሄድ እንመለከታለን።

+ በተፈጥሯቸው መላእክት አያገቡም አይጋቡም። ምክንያቱም ጾታም የላቸው። አንድ ጊዜ እልፍ አእላፋት ወትእልፊተ አእላፋት ተደርገው መቁጠር በማይቻለን መጠን አብዝቶ ፈጥሯቸዋል።

እርሱ ግን እያንዳንዳቸውን በስማቸዋ ያውቃቸዋል። እጹብ ድንቅ ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በአእላፍ ቅዱሳን መላእክት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላምንለክሙ ዘኮንክሙ ሶቤ
እግዚአብሔር በዕለተ ይቤ
አእላፈ አእላፋት ሠራዊት እለ ሱራፌል ወእለ ኪሩቤ
እምሐሩረ መርቄ ወእምቊረ ብዙኅ ምንዳቤ
አክናፊክሙ ይኩናነ ግልባቤ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #ዐሥራ_ሦስት_ወንበዴዎች ስለርሱ በእርሱ ሃይማኖት ከዓለም የተለዩ የከበረ ባፐጸጋ #ቅዱስ_አስከናፍር አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ ከሮሜ መኳንንት አንዱ ሲኾን ምጽዋትን እጅግ ይወዳት የነበረ ደግ ሰው ነው። እርሱም ለድኆችና ለምስኪናን ምጽዋትን የሚሰጥና እንግዶችን ተቀብሎ የሚያስተናግድ ይልቁንም መነኰሳት ቤቱን የሚባርኩለት ደግ ሰው ነው። ይህንም ዜናውን የሰሙ በአገሩ የታወቁ የሚዘርፉ ዐሥራ ሦስት ሽፍቶች ወደርሱ ለመኼድና ያለውንም ኹሉ ለመዝረፍ እርሱንም ለመጉዳት ተማከሩ። ኋላም ሾተላቸውን ስለው የምንኲስና ልብስና ቆባቸውን ደፍተው ወደርሱ ኼዱ፣ እርሱም ከደጃፉ እንዳያቸው ደስ ተሰኝቶ አስተናገዳቸው። እግራቸውንም አጠባቸው። እነርሱንም ዐሥራ ኹለቱን ቅዱሳን ሐዋርያት እንደኾኑ፣ አንዱን ደግሞ ጌታችን እንደኾነ አስቧልና ያንን የእግራቸውን እጣቢ ሠላሳ አምስት ዓመታት ከአልጋ ሳይነሳ መጻጉዕ ኹኖ ለነበረው ልጁ ቢሰጠው በዚያ ድኖ ከአልጋው ተነሳ። 

  + ይህንም ሲመለከቱ እኒያ ዐሥራ ሦስት ሽፍቶች ደነግውጡ። እርሱም ወደነሱ ቀረበና ከእናንተ መኻከል ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የኾነው ይትኛው እንደኾነ ንገሩኝና ልስገድለት አላቸው። የዚህም ተአምር ዜና በአገሩ ተሰምቶ ብዙዎች ሰዎች እየመጡ የነርሱንም ድውያን ወገኖች እንዲያድኑላቸው ይማጸኗቸው ጀመር። እነርሱም የደበቁትን ሾተላቸውን ይዘው አወጡና እኛስ ሽፍቶች ነበርን ልንዘርፍህና ልንገድልህ ነበር አመጣጣችን፣ አሁን ግን ቸሩ አምላክ በሃይማኖትህ ጽናት ምሮናል ብለው ሾተላቸውን ጥለው ከእርሱ ጥቂት ምሥር ወሰዱና የሃያ አምስት ቀናት የእግር መንገድ ተጉዘው ከበረሃ ገቡ። በዚያም የያዙትን ምሥር አዘሩትና ከዚያ በየቀኑ ሦስት ሦስት ምሥር እየፈለጉ እየተመገቡ ለሠላሳ ዓመታት በጽኑዕ ገድል ተጸምደው ኖሩ። 

  + በኋላም አንድ ከሀዲ ንጉሥ ክርስቲያኖችን የሚያሳድድ ተነሣና እሊህን ዐሥራ ሦስቱን ሽፍታ የነበሩ ሰዎች አግኝቶ ገደላቸው። እነርሱም የሰማዕትነትን እና የጽድቅን አክሊል ተቀዳጁ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በእሊህ ቅዱሳንና በቅዱስ አስከናፍር ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለአስከናፍር መንሥኤ መፃጒዕ እምዐራት
ፀበለ ፈያት ነዚሆ በሃይማኖት
ወሰላም ካዕበ ለእሉ ፈያት
እለ ተጋደሉ መጠነ ሠላሳ ዓመት 
ሶበ ነጸርዋ ለዛቲ ትእምርት።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  የሀገረ እንጽና ኤጲስ ቆጶስ የከበረ አባት #አባ_ጢሞቴዎስ አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ አባት ከታናሽነቱ አንስቶ ልቡ ንጹሕ የኾነ ጻድቅ ሰው ነው። ታላቅ ተጋድሎንም የሚጋደል ነው። የእንጽና አገር መንኰንንም በሃይማኖቱ ምክንያት ጽኑዕ ሥቃያትን እያሠቃየ ወደ እሥር ቤት ይመልሰዋል። በየጊዜውም እንዲህ ያደርግበት ነበር። ከእርሱም ጋራ አብረው የታሠሩ ብዙ ሰማዕታት ነበሩ። እርሱም እሊያን ሰማዕታት እየገድላቸአ ቁጥራቸው እስኪያንስ ድረስ የብዙ ሰማዕታትን ንጹሕ ደም አፈሰሰ። እያሠቃየም ገደላቸው። 

  + ከሀዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስን ቸሩ ጌታችን ባጠፋው ጊዜ ታላቁ ጻድቅ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ነገሠ። እርሱም ለአቢያተ ክርስቲያናትና ለምእመናን ነጻነትን አወጀ። በዚህም ምክንያት ይህ ደግ አባት ቅዱስ ጢሞቴዎስም ከእሥር ተፈታ። ከተፈታም በኋላ ለዚያ ሲያሰቃየው ለነበረው ክፉ መኰንን ከጥዋት እስከ ማታ አጽንቶ የሚጸልይለት ኾነ። ይህንም ነገሩን ሰዎች ኺደው ለመኰንኑ በነገሩት ጊዜ፣ እኔስ እንደዚያ አሠቃይቸው ሲረግመኝ የሚኖር ነበር የመሰለኝ፣ እንዲህም ኹኖ ስለኔ ይጸልያልን ብሎ ልቡ በጣም ተነካና አባ ጢሞቴዎስን አስመጣው። የክርስትናንም ሕጓን ያስተምረው ዘንድ ለመነው። አባ ጢሞቴዎስም በሚገባ ቅዱሳን መጻሕፍትን እየተረጎመ አስተማረውና መኰንኑ አመነ። የልጅነትንም ጥምቀት አተመቀው።

  + ከዚህም በኋላ መኰንኑ ክብሩን ቤቱን ትቶ መንኲሶ በገድል ተጸምዶ መኖር ጀመረ። ከአባ ጢሞቴዎስም መንጋዎች ተቆጠረ። አባ ጢሞቴዎስም በቀረ ዘመኑ ኹሉ መንጋዎቹን እያስተማረ በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ኑሮ በሰላም በፍቅር በአንድነት አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ የዚህም አባት በረከት ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለጢሞቴዎስ በገጸ ሰብእ ዘአምኖ
ለእግዚአብሔር አምላክ አድኅኖ
እንዘ ይብል ጸለየ ወሰአለ ለዘኰነኖ
እግዚኦ እግዚኦ ለአበሳሁ ክድኖ
እስመ ለሕይወትየ መርሐ መንገሌከ ኮኖ።

✍️፬-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  የሀገረ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #አባ_ዘካርያስ አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ አባት ከእስክንድርያ ሰዎች ወገን ሲኾን በቤተ ክርስቲያን ንብረት ኹሉ ላይ መጋቢነትና ቅስና ተሾመ። ንጹሕና ድንግልም ነው። በጠባዩም የዋህ ቅን የኾነ በዕድሜውም የሸመገለ ነው። ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ፊላታዎስ ባረፈ ጊዜ ኤጲስ ቆጶሳት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ቀጣዩን ሊቀ ጳጳሳት ለመሾም ተሰበሰቡ። የአባ ፊላታዎስም ማረፍ በተሰማ ጊዜ አንድ ሰው ከንጉሡ የሹመት ደብዳቤ አጽፎ መማለጃም ይዞ እየመጣ እንደኾነ ሰሙ። በዚህም እንዴት የቅዱሳን ሐዋርያት ሥርዓት ይጣሳል ብለው አዝነው ጸሎት ያዙ። ከዚህም በኋላ ይህን አባ ዘካርያስን ከቤተ መቅደስ ጫፍ ላይ በመሰላል ሲወርድ በእንስራ ሆምጣጤ ይዞ ሳለ አድጦት ከጫፍ እስከ ታጭ ድረስ ወርዶ ወደቀ። ነገር ግን እንስራው ሳይሰበር ሆምጣጤውም ሳይፈስ ቀረ። ፈጥኖም ተነስቶ ኼደ። ይህንም ተመልክተአ ምልክት አድርገው ይህን ደግ አባት ሊሾሙት መንፈስ ቅዱስ መራቸው።

  + በርሱም ተስማምተው በእስክንድርያ ኹሉ ላይ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት። ከሹመቱም በኋላ ግን ብዙ ኀዘንና መከራ ተቀብሏል። ከነርሱም አንደኛው፣ አንድ መነኰስ ከአባ መቃርስ ገዳም መጥቶ ኤጲስ ቆጶስነት ሹመኝ አለው። አባ ዘካርያስም መልሶ የቸሩ እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን፣ አንተም ተመልሰህ በገዳምህ በበጎ ገድል ቆይ አለው። ያም መነኰስ ይህችን በጎ ምክር እንደሰማ ተቆጥቶ ወደ ንጉሡ ይኼድና በከንቱ አባ ዘካርያስን ይከሠዋል። ንጉሡም ይዞ አባ ዘካርያስን ማሠቃየት ይጀምርና ለተራቡ አንበሶት ይሰጠዋል። አንበሶቹ ግን አልነኩትም። የአንበሶቹ ጠባቂ ተንኮል የሠራበት መስሎት ይመልስና የላሕም ደም ቀብቶ ዳግመኛ ከተተው አሁንም ምንም አልነኩትም በዚህም ተደንቆ ይዞ ወደ እሥር ቤት ከተተው። ደግሞ ደግሞም እያወጣ ሃይማኖትህን ተው ያለዚያ አሠቃይሃለሁ እገድልሃለሁ ይለዋል፣ አባ ዘካርያስ ግን ምንም ምን አይፈራውም። ኹለተኛም ብዙ ሃብት ገንዘብ እሰጥሃለሁ አለው። አባ ዘካርያስም በዓለም ያለውን ኹሉ ብትሰጠኝም እኔ ሃይማኖቴን አልተውም አለው። ንጉሡም ጥቂት ጊዜ ካሠረው በኋላ ለቀቀው። እርሱም ወደ አባ መቃርስ ገዳም ኼደና በዚያ ቆየ።

  + ክርስቲያኖችም ለዘጠኝ ዓመት በጽኑዕ ሥቃያት ሲሠቃዩ ከቆዩ በኋላ እግዚአብሔር ምሕረት አወረደና ንጉሡም የጠፉት አቢያተ ክርስቲያናት ዳግም እንዲሠሩ ፈቀደ። አባ ዘካርያስም ብዙ አቢያተ ክርስቲያናትን ዳግም አነጸ። ቸሩ እግዚአብሔር አምላክም በእጆቹ ብዙ ገቢረ ተአምራትን አደረገ። ከነዚህም ኹለቱን ብናነሳ፣ አንድ በለምጽ የተመታ ኤጲስ ቆጶስ ነበር። በአባ ዘካርያስ ጸሎትና በዚያም ኤጲ

ስ ቆጶስ ጸሎት ከለምጹ አንጽቶ አድኖታል። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ ድቀት ያገኘው ዲያቆን ነበር። እር

ሱም ከአባ ዘካርያስ እግር ተደፍቶ እያለቀሰ የኾነውን ነገረው። አባ ዘካርያስም ከጨለማ ቤት ዘጋበትና በሦስት በሦስት ቀን ጥቂት ምግብ እየመዘነ ይሰጠዋል። በአርባኛውም ቀን ከለምጹ ፈጽሞ ነጻና ዳነ። እግዚአብሔርንም እያመሰገነ ወደቤቱ ኼደ። ይህም አባት እንዲህ ቸሩን አምላክ አገልግሎ በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በጸሎቱ ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለዘካርያስ ሊቀ ጳጳሳት ዘየሠይመ
እምድኅረ ፊላታዎስ ኖመ
በእንተ ሃይማኖት ርትዕት እንዘ ይትጋደል ፍጹመ
አናብስት ስእኑ በሊዖቶ ሶበ ወገርዎ ፍጽመ
እንዘ ይቀብዑ እንተ ላሕም ደመ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር፣ መጽሐፈ አክሲማሮስ)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱሳን አእላፍ ትጉሃን መላእክት ወበእንተ ቅዱስ አስከናፍር ወቅዱሳን ዐሠርቱ ወሠለስቱ ፈያትውያን ወበእንተ ቅዱስ ጢሞቴዎስ ኤጲስ ቆጶስ ወቅዱስ ዘካርያስ ሊቀ ጳጳሳት ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

t.me @deaconmelakuyifru

ዓርብ 20 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፲፪ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለማር_ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት እና #ለቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቅ፣ #ለቅዱስ_ፊላታዎስ_ሊቀ_ጳጳሳት ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፪ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፪ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ተዝካረ በዓሉ #ለመልአክ_ክቡር_ወግሩም_ማር_ቅዱስ_ሚካኤል_ሊቀ_መላእክት #ርእሰ_ኲሎሙ_ኃይላተ_ሰማይ መሐሪ ወርኅሩኅ ለዘመደ ዕጓለ እመሕያው ወዘይቀውም ኲሎ ጊዜ ቅድመ መንበረ ዕበዩ ለእግዚአብሔር ወይተነብል በእንተ ኲሉ ፍጥረት።

✍️፩-ኅዳር ፲፪ በዚህች ዕለት ለሰው ወገን ኹሉ የሚያዝንና የሚራራ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ኹል ጊዜ በመቆም ለፍጥረቱ ኹሉ የሚማልድ #የመላእክት_አለቃ #በሰማያትም_ለሚኖሩ_ኃይሎች_ኹሉ_አለቃቸው_የኾነ_ለማር_ቅዱስ_ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

  + ይህም ቅዱስ መልአክ በእለተ እሑድ ከተቀጠሩት ግሩማን መላእክት መኻከል የነገደ ኃይላት አለቃ ሲኾን ሳጥናኤል በትዕቢቱ ከመንበረ ክብሩ በወደቀና ጸጋውን በተገፈፈ ጊዜ በነገደ ሳጥናኤልና በሌሎቹም ግሩማን መላእክት ኹሉ ላይ ስልጣት የተሰጠው፣ በትሕትናው የተሾመ የዋህና ደግ ርኅሩኅ ለሚጠሩት ፈጥቶ የሚደርስ፣ ዘወትር ፍጥረቱን ለማስማር ሳይደክም የሚለንምንና የሚራራ፣ መልአከ ምክር የተባለና የቀደመውን እባብ ክፉውን ዲያብሎስን ከሠራዊተ መላኽት ጋር ኹኖ ወደ ጥቅሉ አውርዶ የጣለው ግሩም መልአክ ነው።

  + ይህን መልአክ ክብሩንና ገናንነቱን፣ የተአምራቱን ነገር፣ የርኅራኄውን ነገር እንደምን ይናገሩታል? እንደኔ ያለ በኃጢአት የተዋረደ ሰውማ በምን አንደበቱ ይናገረው ይኾን?

  + በዚህች እለት ቅዱሱ ግሩም መልአክ በቸሩ አምላካችን በእግዚአብሔር ታዝዞ የአሕዛብን ሠራዊቶቻቸውን ኹሉ ደምስሶ ኢያሪኮን ለነቅዱስ ኢያሱ ሊሰጣቸው መጥቶ ተአምራት ያደረገባት እለት ናት። ቅዱስ ኢያሱም ይህን ግሩም መልአክ እንደየመለከተው ደንግጦ በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደልት። መልአኩም አረጋጋው፣ ኢያሱም ጌታዬ ከእኛ ወገን ነህን ወይስ ከጣላቶቻችን ወገን ነህ አለው። መልአኩም መልሶ ኢያሱ የቆምህባት ምድር የተቀደሰች ናትና ጫማህን ከእግርህ አውጣ ብሎ አዘዘው። (ምክንያቱም በዚያ የቆመው የቸሩን የእግዚአብሔርን ስም የተሸከመ ግሩም መልአክ ነውና በፊቱ ራስን ዝቅ ሳያደርጉና የተደከሙትን ኹሉ ነገር ሳይጥሉ መቅረብ አይገባምና) ቅዱስ ኢያሱም እንደተባለው አደረገ። መልአኩም እኔ ለሰማያውያን ኃይላት ኹሉ አለቃቸው ነኝ። የመጣሁት የአሕዛብን ኹሉ ኃይላት ድል አድርጌ ኢያሪኮን ለእናተ እሰጣችሁ ዘንድ ነውና አትፍራ ብሎ አጽናናው። 

  + የቅዱሳን ሰማዕታትን ዜና ሕይወት ልብ ብለን ስናስተውል ደጋግሞ ከሞትና ከሥቃይ የሚያድናቸውንና በመከራ እንዲታገሡ የሚራዳቸውን አንድ መልአክ እናገኛለን። ይኸምው ብዙውን ጊዜ ታላቁ ግሩም መልአክ ማር ቅዱስ ሚካኤል ነው። እርሱም ልባቸውን ለቸሩ አምላክ ስም ሳይሰስቱ ሰማዕታት እንዲኾኑ ጥቡዕ የሚያደርግላቸው ነው።

  + ዳግመኛም ይህ ቅዱስ መልአክ በዚህች እለት ድንቅ ተአምራት ያደረገበትም እለት ነው። ይኸምው ቴዎብስታ የምትባል ሚስት የነበረቸው አንድ ዱራታዎች የተባለ ሰው ነበር። ዘወትርም የዚህን የዋህ መልአክ ዝክር ይዘክሩ ነበር። ኋላ ግን በአካባቢው በተከሰተው ችግር ምክንያት ምንም ምን ለዝክር የሚኾናቸውን አጡ። (ወንድሞቼ እኛስ ሲቸግረን የምንጨነቀው ለምንበላ ለምንጠጣው ነው) ከዚያም ከሚስቱ ጋር ተስማሙና የኹለታቸውንም ልብስ ሽጠው ለዝክር የሚኾን ገንዘብ ለማምጣት ዱራታዎች ልብሶቻቸውን ይዞ ወደ ገበያ ሲኼድና በልውጥ ለማግኘት ብዙ ቢደክም አልኾንለት አለ፣ በዚህም አዝኖ ሊመለስ ሲል ይህ ደግ መልአክ ከመንገድ በመኰንን አምሳል ተገልጠለትና አጽናንቶ በርሱ ስም ዋስ ኾኖለት ከበግ ሻጩ በግ ከዓሣ ሻጩም ዓሣ እንዲወስድና የዓሣውን ሆድ ግን እስኪነግረው ድረስ እንዳይቀድ ነገረው። ከስንዴ ሻጩም እንዲሁ ስንዴ ወሰደ። በኋላም ቤቱ ደርሶ ቢያይ ቤቱ በድንቅ በረከት ተመልቶ አገኘና እጅግ ደስ ተሰኘ። ዝክሩን ከዘከሩ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል ከቤታቸው ተገለጠላቸው፣ (አቤት መታደል፣ ግሩም መልአክን የሚያስተናግድ ቤት ድንቅ ነው!)። ለዱራታዎስም የዓሣውን ሆድ እንዲቀደው ነገረው። በውስጡም ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር አገኘ። እጅግ አደነቀ። መልአኩም ይህን ያደረገላቸው እርሱ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መኾኑን ነገርቅቸው፣ ደንግጠው ከፊቱ ወደቁ፣ አጽናናቸውና ይህን ገንዘብ ያለባቸውን ዕዳ እንዲከፍሉና የቀረውን ለራሳቸው እንዲያደርጎ ነግሮ፣ ዝክሩን እንዳያቋርጡ አዟቸው አረገ። 

  + ይህች እለት በዓለ ሲመቱም ናትና በሚገ'ባ እናከብራት ዘንድ የተገባ ነው። በዚህች እለት ስለፍጡራኑ ኹሉ፣ ስለዝናማት፣ ስለቀላያት፣ ስለነፋሳትና ስለፍጡራን ኹሉ ሰላምን ምሕረትን ይለምናልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በማር ቅዱስ ሚካኤል ጸሎትና ምልጃ ይማረን፣ የመልአኩንም በረከት በኹላችን እጽፍ አድርጎ ያሳድርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም እብል ኪያከ መልአከ
ርኅሩኀ ልብ ለኲሉ እንተ ኢኮንከ ድሩከ
ሚካኤል ሊቅየ ለለእቤለከ
ኅብአኒ በጽላሎትከ ነግሀ ወሠርከ
እስመ እምንእስየ እፈርህ ሀከከ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የታላቁ_ነቢይ_ሰማዕት_ሐዋርያ_ቅዱስ_ዮሐንስ_መጥምቀ_መለኮት ቅድስት ራሱ በደብረ ማህው የታየችበት ነው። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለአስተርእዮትከ ውስተ ደብረ ማህው ዮም
ዘምስለ ዘይት ጥዑም
ቃለ ዓዋዲ ዮሐንስ ዘንብረትከ ገዳም
በትንባሌከ ተፈኒዎ እምሥዋዐ ልዑል አርያም
ሦከ ኃጢአትየ ያውዒ ሚካኤል ፍሕም።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት የኢትዮጵያ ንጉሥ ደጉ ጻድቅ #በእደ_ማርያም የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው።

  + እንዲሁ በዚህች እለት ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ስድሳ ሦስተኛ የኾነ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባት_አባ_ፊላታዎስ አረፈ።

ሰላም ለከ ፊላታዎስ ሐዋርያ
ሊቀ ጳጳሳይ ዘእስክንድርያ
በዕብሬትከ አንፈሱ ሕዝበ ኢትዮጷ
ድኅረ ተሠይመ ላዕሌሆሙ ብእሴ ጒህልያ
እስከ ጽኡላነ ኮኑ ወለፀር ህብልያ።

ሰላም ለከ መሳዌ ኀፃውንት ዘአድማስ
በእደ ማርያም ስኩር ወአኮ በሜስ
ከመ የሀሉ ዝክርከ እንበለ ፈሊስ
እለ ይሜህሩ ሃይማኖተ ሥሉስ ቅዱስ
ደቂቀ ክህነት ወንግሥ ፈረይከ እምከርሥ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ማር ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ወበእንተ ዱራታዎስ ወቴዎብስታ ወበእንተ ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ወቅዱስ ፊላታዎስ ወበእንተ ጻድቅ በእደማርያም ንጉሠ ኢትዮጵያ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

የኅዳር ፲፩ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለቅድስት_ሐና_የአምላካችን_አያት (በሥጋ) እና #ለቅዱስ_ጳኲሚስ፣ #ለቅዱስ_ሚናስ_ሰማዕት ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲፩ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲፩ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ተዝካረ ዕረፍታ #ለቅድስት_ወብፅዕት_ሐና እማ ለእግዝእትነ ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ።

✍️፩-ኅዳር ፲፩ በዚህች ዕለት አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናቷ የኾነች #የተመሰገነች_የቅድስት_ሐና የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው።

  + ይህችውም ቅድስት በኢየሩሳሌም አገር ከሌዊ ወገን ከካህኑ አሮን ትውልድ የሌዊ የሚልኪ ልጅ የኾነ ማጣት ( 'ጣ' ጠብቆ ይነበብ) ልጁ ናት። ለዚህም ለደግ ሠው ማጣት ሦስት ልጆች አሉት። የታላቂቱ ስም ማርያም ነው። ኹለተኛይቱም ሶፍያ ሲኾን ሦስተኛዪቱ ደግሞ ስሟ ሐና ነው። ማርያም የተባለችው ለባል ድረዋት፣ እመቤታችንን ልጇን ከወለደች በኋላ በስደቷ ወራት ኹሉ ስታገለግላት የነበረችውን ቅድስት እናታችንን ሰሎሜን ወለደች። በትውፊት እንደሚነገረውም ይህች የማጣ'ት ልክ ማርያም፣ የእመቤታችን ጠባቂዋ እንዲሆን የተመረጠው የአረጋዊ ዮሴፍ ሚስት ስትኾን ከቅድስት ሰሎሜ ሌላ ወንዶች ልጆችንም ለቅዱስ ዮሴፍ ወልዳለታለች። ዮሳ፣ ያዕቆብ እና ይሁዳ የሚባሉ ናቸው። ዮሳም በስደት እመቤታችንን ልጇን እንዳይገሉባት ኃይለ አንበሳ ተሰጥቶት የብዙ ቀናቱን መንገድ ፈጥኖ ተጉዞ ወታደሮቹን ቀድሞ የወታደሮቹን መቅረብ የተናገረው ነው። እርሱንም ጌታችን እስከ ምጽአቴ ድረስ ይህችን ድንጋይ ተንተራስ ብሎ አሳርፎታል። ቅዱስ ያዕቆብም ከሰባ ኹለቱ አርድእት ወገን ሲኾን በዘመነ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ኤጲስ ቆጶስ ነበር። ይሁዳ ደግሞ በቅዱስ መጽሐፍ አንዲት ምዕራፍ ያላትን ግሩም መልእክት የጻፈልን ሐዋርያዊ አባት ነው።

  + ሶፍያም ደግሞ ለባል ድረዋት ለታላቁ የሙሽራው ወዳጅ የተባለውን፣ በኤልያስ መንፈስ የሚኼደውን መምህር ወመገሥጽ ባሕታዊ ወሰማዕት ሐዋርያ ወነቢይ ማር ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅን የወለደችውን ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደች። ቅድስት ሐና ብፅዕት ደግሞ ከአይሁድ ወገን የከበረውንና ደጉን ቅዱስ ኢያቄምን አጋቧትና የሰማይና የምድር ንግሥት የኾነችውን እመቤታችንን ብቻ ወለዱ።

  + እውነት ላስተዋለው ሰው እንደምን ድንቅ ነው። እንዲህ ያለውን ለሰማይ ለምድር የሚከብድ ስጦታ ንጽሕ ጠብቀው ባይኾንና ቅድስት ሐና እና ቅዱስ ኢያቄም እግዚአብሔርን በእጅጉ የሚያስደስት ምግባር ባይኖራቸው የሔዋን ዕዳ ከፋይ፣ የደቂቀ አዳም ኹሉ ተስፋ፣ በኃጢአት ያጣነውን ንጽሕናና ድንግልና በንጽሓ በመኖር የካሰችልንን እመቤታችንን እንደምን ሊወልዱ ቻሉ? እንደምንስ ደግሞ የአምላካችን አያቶች ሊባሉ ቻሉ?! እፁብ ድንቅ ነው በእውነት። እንግዲህ ልብ ብለን የምናስተውል ከኾነ ከዚህ የምንረዳው ቅድስት ሐና እንደምን ባለ ደስ በሚያሰኝ ገድል ተጸምዳ ትኖር እንደነበር ነው። በሥውር የምትሠራውን የቅድስት ሐናን ገድሏንም እንዳናስተውለው አናውቀውም። ዳሩ ግን ከሴቶች እርሷ እጅጉን ልዕልት እንደኾነች እናውቃለን። እንግዲህ ከሴቶችን ኹሉ እጅጉን የሚበልጥ ትሩፋትና ገድል ባይኖራት እንደምን የአምላካችን አያቱ ልትባል በቃች? ስለርሱ በጥልቅ ለመናገር ግን ከኃጢአታችንም የተነሳ ተሠውሮናልና ታላቅነቷን ግን ሳንጠራጠር በማድነቅ እናመሰግናታለን።

  + ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በጸሎቷ ይማረን፣ በቅድስት ጸሎቷ የሚገኝ በረከትም እጽፍ ድርብ ይሁንልን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለኪ ለጸሎተ ኲሉ ምዕራጋ
ከመ አስካለ ወይን ዲበ ሐረጋ
ሐና ብፅዕት ተፈስሒ እንበለ ንትጋ
እስመ ረከብኪ ሞገሰ ወአድማዕኪ ጸጋ
እምሔውተ አምላክ ትኩኒ በሥጋ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ኹለተኛ #የአርኬላዖስ_ሰማዕት #የአበ_ምኔት_ኤልሳዕ ዳግመኛም #የመነኰስ_ጳኲሚስና #የሰማዕት_ማር_ቅዱስ_ሚናስ መታሰቢያቸው ነው። በረከታቸውም በዝታ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለአርኬላዖስ ሰማዕት
ወኤልሳዕ አበ ምኔት
ወምስሌክሙ ጳኲሚስ ኅቢረ ሥርዓት
ጸልዩ በእንቲአየ ክቡራን ኖሎት
እስመ እመንሱት ያድኅን ጸሎት።

ሰላም ለከ ፈጻሜ ሕማማት በኃሠሣ
ዐቢየ ሃይማኖት ሚናስ እምውሉደ ቅድስት ከኒሳ
ወሰላመ እብላ እንዘ እዌድሳ
ለእምከ አውራንያ እንተ አዕረቅዋ ልብሳ
ወዘቀሠፍዋ ዘባና ወዘርሣ።  

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅድስት ወብፅዕት ሐና ወቅዱስ አርኬላዖስ ወቅዱስ ኤልሳዕ አበምኔት ወበእንተ ቅዱስ ጳኲሚስ ወቅዱስ ማር ሚናስ ዐቢይ ሰማዕት ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

ረቡዕ 18 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፲ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለቅድስት_ሶፍያና_ለደናግል_ሰማዕታት እና ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፲ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፲ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮና ሰማዕተ #ደናግል_ቅዱሳት_መነኰሳይያት_ንጹሐት #ወእሞን_ሶፍያ።

✍️፩-ኅዳር ፲ በዚህች ዕለት #ቅዱሳት_ንጹሐት_መነኰሳይያት_ደናግል #እናታቸው_ሶፍያም በሰማዕትነት አረፉ።

  + ይህም የኾነው እሊህ ቅዱሳት ደናግል ከተለያየ አገር መለኮታዊት ፍቅር ጠራቻቸውና ተሰባስበው በሮሜ ካሉ ገዳማት በአንዱ የምንኲስናን ልብስ ለብሰው ይኖሩ ነበር። ለነርሱም ቅድስት ሶፍያ የተባለች እመምኔት ነበረቻቸው። እርሷም በበጎ ምግባር የተሸለምውች ናትና ልክ እንደንጹሐን መላእክት እስኪኾኑ አደረሰቻቸው። ከነርሱ መኻከል አረጋውያን የኾኑ ሲኖሩ እንዲሁ ደግኖ ልጅ እግር የኾኑ ወጣቶችም አሉ። 

  + ከጊዜም በኋላ ከሀዲው ንጉሥ ዑልያኖስ ከፋርስ ንጉሥ ከሳቦር ጋራ ሊዋጋ በሮሀ በኩል ሲያልፍ በመንገድ ይህን ገዳም ይመለከትና ስለምንነቱ ይጠይቃል። የደናግል ገዳም መኾኑን በነገሩት ጊዜ ወታደሮቹን ልኮ አወደመው፣ መነኰሳይያቱንም ከቅድስት እመምኔታቸው ሶፍያ ጋራ በአንድነት የሰማዕትነትን አክሊል ተቀበሉ። ንጉሡንም ደግሞ ታላቁ ኃያል ሰማዕት ቅዱስ መርቆሬዎስ በዐፀደ ሥጋ ኼዶ በጦሩ ወግቶ ገደለው። እርሱ በሥጋ በነፍስ ሲጎዳ እሊያ ሰማዕታት ግን በነፍስ ተጠቀሙ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በሰማዕታቱ ጸሎት ይማረን፣ በረከታቸውም እጽፍ ድርብ ኾና ትደርብን።

ሰላም ለደናግል እምተደልዎ ወእምተሐውዞ
ለወልደ ማርያም ድንግል እንዘ ይተልዋ ግዕዞ
ሶበ ዑልያኖስ ቀተሎን ለእሎን በተጋዕዞ
እግዚአብሔር መስተበቅል ለመርቆሬዎስ አዘዞ
በቀለ ደሞን በኲናት ይርግዞ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት በድሜጥሮስ ዘመን #ስለጾም_ሥርዓት ቅዱሳን #ሊቃነ_ጳጳሳት_የአንድነት_ስብሰባ አደረጉ።

  + ይህም የኾነው ቀድሞ የጌታችን በዓላትና አጽዋማት ያለ ቀመር እንዲሁ በዋለበት ቀን ነበር የሚከበረው። በኋላ ግን በእስክንድርያ ይህ ቅዱስ ድሜጥሮስ ከመጣ በኋላ ሱባኤ ገብቶ ልዩ የኾነውን የባሕረ ሐሳብን ቀመር ቀምሮ አሰናዳ። የጌታችንን አጽዋማትና በዓላት ከሠራ በኋላ ለሌሎች አገራትም ኤጲስ ቆጶሳት ላከው። እነርሱም መልእክቷን በተመለከቱ ጊዜ ደስ ተዘኙበት። 

  + የሮሜውም አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦር መልእክቱ እንደደረሰው ተመልክቷት ደስ ተሰኘባት። ለአንጾኪያውም ሊቀ ጳጳሳት አባ መክሲሞስ ላከ። ወደ ኢየሩሳሌሙም ሊቀ ጳጳሳት ወደ አባ አጋብዮስ ላከ። እነርሱም ኹላቸው ባነቡት ጊዜ ደስ ተሰኙባቸው። የሮሜው ሊቀ ጳጳሳት አባ ፊቅጦርም በሮሜ ያሉትን ኹሉ ኤጲስ ቆጶሳት ስብሰባ ጠርቶ በሊቃውንቱ ኹሉ ፊት አነበቧት። ደስም ተሰኙባትና የአጽዋማትና የበዓላትን ነገር በርሷ ለማስተካካል። ለግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለክሙ ካህናተ ስባሔ ወዘምሮ
ዘአፍጠንክሙ ሐዊረ እንበለ ተድኅሮ
ውስተ አሐዱ መካን ለተጋብኦ ወለአማኅብሮ
ሐሳበ አበቅቴ ዘመንፈስ ቅዱስ መሀሮ 
እምነ ድሜጥሮስ አብ ትንስኡ አእምሮ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  #የጳውሎስና #የሦስት_ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው። በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅድስት ሶፍያ ወቅዱሳት ደናግል መነኰሳይያት ወበእንተ ቅዱሳን ኤጲስ ቆጶሳት ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

ማክሰኞ 17 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፱ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለጉባኤ_ኒቅያ #ለቅዱስ_ይስሐቅ_ሊቀ_ጳጳሳት እና ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፱ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፱ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ አዕረፈ አብ #ቅዱስ_ይስሐቅ ሊቀ ጳጳሳት ዘእስክንድርያ።

✍️፩-ኅዳር ፱ በዚህች ዕለት የእስክንድርያው አገር አርባ አንደኛው #ሊቀ_ጳጳሳት_ቅዱስ_ይስሀቅ አረፈ።

  + እህም ቅዱስ ቡርልስ ከሚባል አገር ነው። ወላጆቹም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ባለጸጎች ናቸው። ይህንም ቅዱስ ከወለዱት በኋላ ኤጲስ ቆጶሱ ሲያጠምቀው በሕፃኑ ራስ ላይ የብርሃን መስቀል ምልክት አየ፣ ስለርሱም በቤተ ክርስቶያን ታላቅ ሹመትን እንደሚሾም ትምቢት ተናገረለት። ኋላም ጥቂት እንዳደገ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርትና ጽፈትን አስተማሩት። የቅዱሳንንም ዜና ሕይወት የሚያነብ ኾነ። ከዚያም ወደ አስቄጥስ ገዳም ገባና ከአበ ምኔቱ ከአባ ዘካርያስም መነኰሰና በገድል ተጸመደ።

  + በሌላም ጊዜ አንድ ጻድቅ ሰው ይህን ቅዱስ ይስሐቅን በቤተ ክርስቲያን አየውና በቤተ ክርስቲያን ላይ ታላቅ ሹመትን እንደሚሾም ተነበየ። በዚያም ወራት ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ዮሐንስ ጸሕውፊ ፈለገና ቅዱስ ይስሐቅን አስመጣው። ቅዱስ ይስሐቅ ግን ወደ ገዳም መመለስ ይሻ ነበርና ጽሑፉን አበላሸው። ሊቀ ጳጳሳቱም ከርሱ ሊለየው ወዶ እንዲህ እንዳለ ያውቃልና እንደማይተወው ነገረው። ይህን ባወቀ ጊዜ ቅዱስ ይስሐቅም በሚገባ አሳምሮ ጻፈ። አባ ዮሐንስም በርሱ ደስ ተሰኘበት። ከርሱ በኋላም ስለሚሾመው ሊቀ ጳጳሳት ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክት አባ ይስሐቅ እንደተካው ተነገረው። ይህንም ለሕዝቡ ኹሉ ነገራቸው። በኋላም አባ ዮሐንስ ልክ እምዳረፈ በርሱ ፈንታ ቅዱስ ይስሐቅን ሾሙት። በርሱም የጵጵስና ዘመን ቤተ ክርስቲያን እንደማኅቶት አበራች። በማርቆስም፡ወንበር  ሰባት ዓመት ተኩል ሲኖር እግዚአብሔርን በበጎ አገልግሎ በሰላም አረፈ። እርሱም ብዙ መከራዎችን ታግሦ ተቀብሏል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በቅዱስ ይስሐቅ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የሦስት_መቶ_ዐሥራ_ስምንቱ ኤጲስ ቆጶሳት በኒቅያ የተሰበሰቡበት ነው።

ሰላም ለጳጳሳት እለስኖሙ አብርሀ
በሀገረ ኒቅያ ወአድያሚሃ
አፍራሰ ሕይወት እሉ በብሂል ዕንቋዕ ዘበፍስሓ
ዘኬዱ ውስተ ባሕር ወዘወረዱ
እንዘ የሐምጉ ማያተ ብዙኀ።
 
(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱሳን ሠለስቱ ምዕት ዐሠርቱ ወሰምንቱ ርቱዓነ ሃይማኖት፣ ወበእንተ ቅዱስ ይስሐቅ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

ሰኞ 16 ኖቬምበር 2020

#ሰይጣናት_ስንኳ_ስለ_ተገዙላችሁ_በዚህ_ደስ_አይበላችሁ

¶ "በቃላችን በአጋንንት ላይ ስሉጥ በኾነና ከፊታችንም አጋንንቱ ፈርተው ደንግጠው በሸሹ ጊዜ፣ አጋንንትን ስለ ገሠጸ እና እነርሱም ስለ ተገዙለት ማንም ሰው አይደነቅ። በእጆቹ እንዲህ የመሰሉ ነገሮችም በማይደረጉለት ሰውም ላይ ከቶ በንቀት አይነሳሳ፤ ኾኖም ከኹሉ አስቀድሞ የተለያዩ ሰዎችን ሕይወቶች እና ምግባራት ይመርምር ያስተውልም እንጂ። ከዚህም ጥልቅ ምርምር አምላካዊት ጸጋ ከማን ጋር እንደምትኖር እና የእግዚአብሔርም ጽድቅ በማን ላይ እንደያርፍ ያስተውላል፤ እነርሱም ደግሞ አጋንንትን ከሚያስወጡት ይልቅ የሚበልጥ መስተዋት ይኾንልናልና። ሰነፍ ሰው የአጋንንቱን ርኲሰታቸውንና ስለዚህም ደግሞ እንደሚገሠጹ መመልከት ሲቻለው፣ ደጎቹ ሰዎች ግን የአጋንንቱን አሠራራቸውን በሚገ’ባ መመርመር ይችላሉ። ከዚያም በተጋድሏቸው ይበረታሉ። አንድ ሰው የተከናወነ ፍጹም ገድለኛ መኾኑም ይኹን የተናቀ ሽቁጥቁጥ መኹኑ የራሱ ድርሻ ነው። በአጋንንት ላይ እጆቹን መዘርጋቱና የእነርሱም ከሥፍራው መሸሽ ግን የርሱ አይደለም፤ የሰማያዊት ጸጋ ነው እንጂ። ደቀ መዛሙርቱ እንዲሰብኩ የተላኩበትን ቅዱስ ወንጌል ሰብከው በደስታ ወደ ጌታቸው በተመለሱ ጊዜ፣ አጋንንትም እንኳ ለቃላቸው ስለ ተገዙላቸው ተደስተው ነበር። እንኪያስ ማንም ማስተዋል ያለ’ው ሰው ይኽንን ለእነርሱ የተሰጠውን መልስ ይመልከት፤ ያድምጥም። «ሰይጣናት ስንኳ ስለ ተገዙላችሁ በዚህ ደስ አይበላችሁ። ነገር ግን ስማችሁ በሰማያት ስለ ተጻፈ በዚህ ደስ ይበላችሁ እንጂ»/ሉቃ ፲፡፳/። እንግዲህ የስሞች በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ መጻ’ፍ እግዚአብሔርን በሚያስደሰት ምግባር ለመገ’ኘት ምስክር እና ለዚህም ነገር ለተገ’ቡት ደግሞ የቀና ልቡና ነው፤ በአጋንንት ላይ ያለ’ ስልጣን ግን በግልጥ የቤዛችንን ጸጋ [ትእምርት] ነው።" ¶

#ማኅቶተ_ገዳም (ገጽ 72-73)

እሑድ 15 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፯ ዝክረ ቅዱሳ

እንኳን #ለማር_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ዘልዳ እና #ለቅዱስ_አባ_ናህርው፣ #ለቅዱስ_ሚናስ_ኤጲስ_ቆጶስ_ዘሀገረ_ተመይ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፯ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፯ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮነ ሰማዕተ #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_እስክንድርያዊ።

✍️፩-ኅዳር ፯ በዚህች ዕለት #የእስክንድርያው_ቅዱስ_ጊዮርጊስ በሰማዕትነት አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ አባቱ በእስክንድርያ በንግድ የሚኖር ሲኾን ልጅ አልነበረው። በዚህችም እለት በኾነቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ልዳዊ ክብረ በዓል ልጅ እንዲሰጠው ከአምላኩ ያማልደው ዘንድ ማር ቅዱስ ጊዮርጊስ ልዳዊን ተማጸነው። ልመናውንም ሰምቶ ልጅ ሰጣቸውና ስሙን በዚህ ልዳዊ ሰማዕት ስም ጊዮርጊስ አሉት። የዚህም እናቱ ለእስክንድርያው አስተዳድስሪ ለአርማንዮስ እኅቱ ናት፣ በኋላም እናንትና አባቱ ሲያርፉ ከእናቱ ወንድም ጋራ ኖረ። ሃያ አምስት ዓመት ዕድሜ በኾነውም ጊዜ ለድኆች የሚራራ ምጽዋትን የሚያዘወትር ደግ ኾነ። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ዘወትር ይገሠግስ ነበር። 

  + ለመኰንኑም አንዲት ሴት ልጅ ነበረቸው። እርሷም እየተዘዋወሩ መጎብኘትን ትወድ ነበርና አንድ እለት በደብረ ቊስቋም ስትዘዋወር በዚያ አካባቢ መነኰሳቱ ጣዕም ባለው ምስጋና ሲያመሰግኑ በዚያ ልቡናዋ ተመሰጠ። ኋላም ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠይቀው እርሱ ተረጎመና አስተማራት። በልቡናዋም አመነች። ወደ አባትዋም ስትመለስ በክብር ባለቤት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አመነች። አባትዋም ሊያባብላት ብዙ ቢሞክር አልሳካለት አለ። በኋላም አሠቃይቶ በመጨረሻም ራሷን በሰይፍ አስቆረጣት።  ቆይቶም ሰዎች ይህን ያደረገውና የልጅቷን ልቡና የለወጠው ያስተማራት ቅዱስ ጊዮርጊስ መኾኑን ነገሩት። እርሱም አስቀርቦ አሠቃየው። ደግሞም ወደ እንጽና አገር ላከውና በዚያ አሠቃይተው ራሱን በሰይፍ ቆረጡት። በኋላም ሳሙኤል የሚባል ዲያቆን ቅድስት ሥጋውን ወደ መኑፍ አገር ወሰደው። የአርማንዮስም ሚስት ባወቀች ጊዜ አስመጣችውና ከልጅዋ ሥጋ ጋር በአንድነት በእስክንድርያ አገር አደረገችው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በሰማዕቱ ጸሎት ይማረን፣ በረከቱም በዝታ ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ዕብል ሥቃየከ ዕጹበ
ጊዮርጊስ ዘኮንከ ስመ ሊቀ ሰማዕት ውሁበ
መኰንን አብድ ዘኢየአምር ጥበበ
በጊዜ ኮንከ ስምዐ ወለትምህርተ ክርስቶስ አበ
ርእሰ ወለቱ አምተረ ወርእሰከ ካዕበ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ከግብጽ አገር ከፍዩም መንደር #ቅዱስ_አባ_ናህርው በሰማዕትነት አረፈ።

  + ይህ ቅዱስ እግዚአብሔርን እጅግ የሚፈራው ነው። በእስክንድርያም አገር የሚሠቃዩ የሰማዕታትን ዜና በሰማ ጊዜ ክብር ይግባውና ስለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለስሙ ሰማዕት ሊኾን ወደደ። እንዲሁ ደግሞ በራእይ ወደ አንጾኪያ ኺደህ ሰማዕት ትኾን ዘንድ አለህ አለው። ወደዚያ እንዴት መድረስ እችላለሁ ብሎ በሚያስብ ጊዜ ቸሩ አምላካችን ለስሙ ስግደት ይኹንና መልአኩን ቅዱስ ሚካኤልን ላከለትና እርሱ በክንፎቹ ተሸክሞ አንጾኪያ አደረሰው። በዲዮቅልጥያኖስም ፊት ቆሞ በእግዚአብሔር ስም ታመነ። ንጉሡም ስሙንና አገሩን ከጠተቀው በኋላ ለጣዖት እንዲሠዋ ሊያግባባው ቢሞክርም አልሞነለትም። የገባለትንም ቃል ኹሉ አቃለለበት። ኋላም ንጉሡ ጽኑዕ ሥቃይን እንዳላሠቃይህ የምልህን ድማ ቢለውም እርሱ ለሃይማኖቱ ጨክኗልና ክፉ ምክሩንም ኾነ ማስፈራራቱም አልሰማውም።

  + በኋላም ቅዱስ ናህርውን በብዙ ዓይነት ሥቃይ እንዲያሠቃዩት ንጉሡ አዘዘ። ለአንበሶች ጣሉት እነርሱ ግን ምንም አልነኩትም። ከእሳትም ጨመሩት እሳቱም ከቶ አልነካውም። ቀጥለውም በወጭት አድርገው ቀቀሉት፣ በደህና ወጣ። ንጉሡም ማሠቃየትን በሠለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡት አዘዘ። ይህም ቅዱስ አባት አባ ናህርው በአንጾኪያ ሰማዕት መኾኑም የአንጾኪያ ሰማዕታት ኹነው በእስክንድርያ ሰማዕት በመኾናቸው በነርሱ ፈንታ ነው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ሰላም ለብእሲ ፍንው
በክንፈ ሚካኤል ዐውደ ዲዮቅልጥናኖስ ዕልው
ለዝ ሰማዕት አባ ናህርው
ጤገን ሥእነ አውዕዮቶ ዘአፍልህዎ በሐው
ወኢነከይዎ አናብስት ዘበድው።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  ከገምኑዲ አውራጃ የሀገረ ተመይ ኤጲስ ቆጶስ #የአባ_ሚናስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ኾነ።

  + የዚህም ቅዱስ ወላጆች ደጎች እግዚአብሔርን የሚፈሩ ዜናቸውም በቅዱዳን አባቶች ዘንድ እስከተሰማ ድረስ በጾማቸው በጸሎታቸው በገድል በመጸመዳቸው ልክ እንደመነኰሳት #የመነኰሳትን_ሥራ_የሚሠሩ ናቸው። እነርሱም ይህን ልጃቸውን ካለፈቃዱ ሚስትን አጋቡት። ሙሽራይቱም ወፋለችበት ጫጉላ ገባና ከእርሷ ጋራ በንጽሕና በድንግልና ለመኖር ተድማሙ። ኹለቱም በጽንዕ ገድል ይጋደሉ ጀመር። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ሚናስ የምንኲስናን ልብስ ሊለብስ ወዶ ሚስቱን በዚህ ዓለም እያለን የምንኲስናን ሥራ ልንሠራ እንደምን ይቻለናል አለ። ከዚያም ከልብሳቸው ውስጥ ማቅ በመልበስ በእግዚአብሔር መንፈስ የተደረሱ ቅዱሳት መጻሕፍትንም በማንበብና ለጸሎት በመትጋት ሌሊቱን ኹሉ ይቆሙ ነበርና ከዚህም በኋላ ሰላምታ ሰጥታ በል ደህና ኹን ብላ ወደ ገዳም እንዲኼድ ሸኘችው። እርሱም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ኼደና ከወላጆቹ ሊርቅ ወዶአልና እነርሱም ወደ ሚስቱ ሊመልሱት ብዙ ቢደክሙም ሊያገኙት አልቻሉም። እግዚአብሔርም እንዳያገኙት ሠውሮታልና። እርሱም በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳዳት የኾነው አባ ሚካኤል ከእርሱ ጋር በምንኲስና ነበር። ከዚህም በኋላ ኹለቱ ብሩሃን ከዋክብት #አባ_አብርሃምና #አባ_ገዓርጊ በነበሩበት ወራት ወጥቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ኼደ። ለእኒህም ቅዱሳን ልጅ ኾናቸውና በገድል ላይ ገድልን እየጨመረ በምንኲስናው ገድሉን ቀጠለ። ከነርሱም ትምህርታቸውንና የገድል ጎዳናቸውን በብዙ ይማራል፣ ከብዙዎች በተጋድሎውና ለእግዚአብሔር በመገዛቱ ከፍ ከፍ አለ። አባ ገዓርጊና አባ አብርሃም ሌሎቹም አበው ከገድሉ የተነሳ ደስ ይሰኙበትና ያደንቁ ነበር። ሰይጣን ግን በርሱ ቀንቶበት በታላቅ አመታት መታው (ደበደበው) ኹለት ወርም በምድር ላይ ወድቆ ኖረ። ከዚህም በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ባለ ጤና አድርጎ አስነሳው።

  + ኤጲስ ቆጶስም እንዲኾን የክብር ባለቤት ቸሩ ጌታችን መርጦታልና የሊቀ ጳጳሳቱ መልእክተኞች መጡ። እርሱም ከአበው መነኰሳት ሊለይ በመኾኑ እጅግ ኀዘን ገባው። ቅዱሳኑም ይህ የእግዚአብሔር ሥራ ነውና አትዘን አሉት። እርሱም ራሱ ለእግዚአብሔር ታእዛዝ ራሱን ዝቅ አድርጎ በጽኑዕ የሚገዛ ኾነ። ሊቀ ጳጳሳቱም በተመይ አገር ላይ ኤጲስ ቆጶስነት ሾመው። ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት በሽተኞችን የሚፈውሳቸው ሆነ፣ በሽታ ያለባቸውም ኹሉ ወደርሱ ይመጣሉ እርሱም ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር በምጸለይ ይፈውሳቸዋል።

  + ኹለተኛውም ይርተሠወረውን የማወቅ ሀብተ ጸጋ እግዚአብሔር ሰጠው። ከደግነቱና ከጸጋው የተነሳ ብዙዎች ኤጲስ ቆጶሳት ወደርሱ እየመጡ ከርሱ በታች ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይገዙለት ነበር። እርሱ በሲመታቸው ጊዜ እጁን ጭኖባቸዋልና #እለእስክንድሮስ #ቆዝሞስ #ቴዎድሮስና #ሚካኤል ለሚባሉ ሊቃነ ጳጳሳት አባት ኾነ። የሚያርፍበትንም ቀን በመንፈስ ቅዱስ ባወቀ ጊዜ ሕዝቡን ሰብስቦ በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ አስተማራቸው፣ አዘዛቸው። ለጌታችንም አደራ ሰጣቸው። ከዚህም በኋላ ወደ ወደደው ወደ እግዚአብሔር ኼደ። እያዘኑም በክብር እርሱ ካዘዛቸው ቦታ አኖሩት። ለእግዚአብሔር

ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በጸሎቱ ይማረን፣ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለከ ሚናስ ኅሩይ
ኤጲስ ቆጵስ ዘሀገረ ተመይ
በእንተ ዘአንጻሕከ ሥጋከ ወልቡናከ እምጌጋይ
ከመ ታእምር ኲሎ ውስተ ልበ ሰብእ ዘይትሔለይ
መጽሔተ አእምሮ ነሣእከ እምልዑል ሰማይ።

✍️፬-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  የልዳ ሀገር የኾነው #ሊቀ_ሰማዕታት #ማር_ቅዱስ_ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ድንቅ ተአምርም ያደረገበት መታሰቢያው ነው።

  + ይህም የኾነው ድንቅ ተአምራት የሚደረግባት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነበረችና ክፉው ከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ሊያፈርሳት ፈለገና መኰንኑን ላከው። መኰንኑ አውህዮስም ከቤተ ክርስቶያኒቱ ገብቶ ብዙዎችን በድፍረት ሲገለባብጥ ከሥዕለ አድኅኖው ዘንድ የነበረውን በብርጭቆ የተሠራ መቅረዝ ቢነካው ወርዶ ራሱን በጥብጦ ጣለው። እርሱ ክፉ አሟሟትን ሲሞት አገልጋዮቹ ወስደው ወደ ባሕር ጣሉትና በኃፍረት ወደ አገራቸው ተመለሱ። ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስም በዚህ ተመሳጭቶ ራሴ አፈርሰዋለሁ ብሎ ቦመጣ የቤተ ክርስቲያኑ ደወል መሃል አናቱን በጥብጦ ጣለው። አንድም የታዘዘ መልአክ መጥቶ ዓይኑን አተፋው፣ ታውሮም ለሰባት ዓመታት ቁራሽ እየለመነ ከኖረ በኋላ፣ ጌታችን የቤተ መንግሥቱን ሰዎች አስነሳበትና በክፉ አሟሟት ሞተ። ጻድቁ ቈስጠንጢኖስም ነገሠ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በቅፉስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት ጸሎት ይማረን፣ በረከቱም በዝታ ትደርብን ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም እብል ለዘአርአየ ትእምርቶ
በልዳ ሀገር በጊዜ ቀደሱ ቢቶ
ጊዮርጊስ መዋዒ ቃለ ጽራህየ በኢያስትቶ
ከመ እስሐብ ፀረ ነፍስየ ይመጥወኒ ቅናቶ
ወለደርብዮቱ ፍጹመ ስሑለ ኲናቶ።

✍️፭-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #ዘኖቢስና እናቱ #ዘኖቢያ በሰማዕትነት አረፉ።

  + እኒህም ቅዱሳን ተበይስ ከምትባል አገር ከታላላቆቿ ናቸው። ክርስቲያንም በመኾናቸው በንጉሡ ፊት ከሠሷቸው። ንጉሡም አስቀርቦ አገራቸውንና የሃይማኖታቸውን ነገር መረመራቸው። እነርሱም በኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚያምኑ መሰከሩ። መንኰንኑም ይህን ሲሰማ ተቆጣ፣ ልብሳቸውንም ገፍፈው በአደባባይ በጠጉርቅቸው ሰቅለው እንዲደበድቧቸው አዘዘ። ቢጸልዩ ማሠሪያቸው ተፈትቶላቸው የብርሃን ልብሶችን ለብሰው ተገኙ። ሕዝቡም ይህን ድንቅ ተመልክተው ጌታችን የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገኑት።

  + መኰንኑ ግን ተቆጥቶ እርስ በርስ እንዲተያዩ አድርጎ በመስቀል ሠቀላቸው፣ በእግዚብሔርም ቸርነት ምንም ምን ሳይኾኑ፣ እንዲያውም የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምሩ መኰንኑ አገኛቸው። ሕዝቡም አይተው እና እየጮኹ በአንድ ቃል አመሰገኑ። ኹለተኛም በስጣቸው የብረት ችንካሮች ያሉባቸውን ኹለት ወንበሮችን እንዲያዘጋጁ አዘዘና በዚያ ላይ አስቀምጠዋቸው በእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመሯቸው። ከዚያም ግን በደህና ወጡ። መኰንኑም የውሽባ ቤቱን ጠባቂ ቅዱሳኑን እሳት አንድዶ በውስጡ እንዲጨምራቸው ነገረው። ከዚሃም በደህና ቢወጡ መኰንኑ የሚያደርጋቸውን ነገር ግራ ቢገባው እንዲገድሏቸውና አቃጥለው በነፋስ ውስት እንዲበትኗቸው አዘዘ። በገደሏቸውም ጊዜ ነጐድጓድና መብረቅና ንውጽውጽታ ዝናምም ኾነ።  ብዙዎች ኃምሥ አራት ያህል ሰዎች ሞቱ። በሌሊትም ምእመናን መጥትወ በስውር ወሰዷቸው። በማግስቱም መኰንኑ ሲመጣ በሥጋቸው የኾውን ተአምር ነገሩትና በጌታችን አምኖ ክርስቲያናዊ ኾነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እናንም በጸሎታቸው ይማረን፣ በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለዘኖብያ ወለዘኖቢስ በኲራ
እለ ተወክፉ ምንዳቤ ወተዓገሡ መከራ
አመ በእሳት ፈቀደ ለነፍሶሙ ያጽዕራ
መኰንነ ሀገር አስተርአየ ማዕከለ ብዙኃን ሐራ
ዐቃቤ ብለኔ ከዊኖ እንዘ ይፀውር ኮራ።

ሰላም እብል ሰማዕታተ ብዙኃነ
ምስለ ዘኖቢስ ወዘኖቢያ ዘአስተኃፈሩ ሰይጣነ
ፈጺሞሙ ስምዐ በጊዜ ለብሱ ግዕዛነ
ሶበ ነጐድጓድ ወመብረቅ ኮነ
ምስለ ሐራሁ መኰንን አምነ።

✍️፮-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  ቅዱሥን #ሐዲስ_መርቆሬዎስና ወንድሙ #ዮሐንስ በሰማዕትነት አረፉ።

ሰላም ለመርቆሬዎስ ዘተጋደለ ፈድፋደ
ወለዮሐንስ ምስሌሁ ለአርዑተ ሥቃይ ዘተጸምደ
አመ ወረውዎሙ ሐራ ድኅረ መተሩ ክሣደ
እሳት ውዑይ በድኖሙ ኢያንደደ
እስመ ረከብዎሙ ድኁናነ እምከዊን ሐመደ።

ሰላም እብል ክልኤተ አስካለ
እምሐረገ ወይን ዘበዐፀደ መርዔት በቈለ
አንከሩ ጉባኤ ዘክልኤሆሙ ኃይለ
ድኅረ ተመትረ ሰሚዖሙ እምርእሰ ዮሐንስ ቃለ
ወእምርእሰ መርቆሬዎስ ነጺሮሙ በክሣዱ ስቁለ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ ጊዮርጊስ እስክንድርያዊ ወበእንተ ቅዱሳን ዘኖቢያ ወዘኖቢስ ወበእንተ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሐዲስ ወቅዱስ ዮሐንስ እኁሁ፣ በእንተ ቅዱስ ሚናስ ሊቀ ጳጳሳት ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

ቅዳሜ 14 ኖቬምበር 2020

የኅዳር ፮ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለቅዱስ_ፊልክስ እና #በዓለ_ቊስቋም፣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፮ ዝክረ ቅዱሳን።

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፮ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ቦአ እግዚእንው ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት ውስተ #ደብረ_ቊስቋም ምስለ እግዝእትነ ቅድስት ድንግል ማርያም ወዮሴፍ አረጋዊ ወሰሎሜ በጊዜ ተመይጦቶሙ እምስደት ወአዕረፉ እምፃማ ፍኖት።

✍️፩-ኅዳር ፮ በዚህች ዕለት ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎምከ ጋር ከስደት በሚመለሱ ጊዜ ወደ #ደብረ_ቊስቋም ገባ፣ በመንገድ ጒዞ ካገኛቸውም ድካም አረፉ።

  + ዳግመኛም በኋላ ዘመን በዚህ በደብረ ቊስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቶቹን ሰበሰባቸው፣ ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቊርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወገኖቹ ሰጣቸው። ለዚህም የእስክንድርያ አገር ሊቃነ ጳጳሳት ቅዱሳን አባቶቻችን ቄርሎስና ቴዎፍሎስ ምስክሮችን ሆኑ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ አምላክን የወለደች የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በረከቷ ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለአእጋሪከ ውስተ ደብረ ቊስቋም እለ ጌሣ
ሕፃነ ማርያም ክርስቶስ አመ ጐየይከ ደወለ ንሒሳ
ወአመ በጽሐ ህየ እንዘ ይነሥእ ኃይለ አንበሳ
እንተ ሠመርከ በኅድዓት ለነፍሱ ታፍልሳ
ሰላም ሰላም ለወልደ ዮሴፍ ዮሳ።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባት_ፊልክስ አረፈ።

  + ይህም ቅዱስ ወላጆቹ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው። የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማሩት፣ የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት አባ አንስጣስዮስም ዲቁና ሾመው። ኋላም የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ዮስጦስም የዚህን ቅዱስ በጎ ጠባዩንና የጽድቁን የትሩፋቱን ደግነት ተመልክቶ ቅስና ሾመው። እርሱም በአገልግሎቱ የተመሰገነ ደግ አባት ነበርና ከርሱ በፊት የነበረው ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ በአረፈ ጊዜ ይህን አባት መረጡይ፣ በእግዚአብሔርም ፈቃድ በሮሜ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት። እርሱም የቸሩን አምላክ መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው።

  + ትሩስ ቄሣርም ሲሞት፣ ከርሱ በኋላ ቴዎድሮስ ቄሣር ነገሠ። እርሱም ክርስቲያኖችን ያስጨንቅና ያሠቃይ ጀመር። ብዙዎችም ከእጁ ሰማዕትነትን ተቀበሉ። ይህም ደግ አባት ከዚህ ክፉ ከሀዲ ንጉሥ ብዙ ኀዘንና መከራ ተቀብሏል። ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቢያመለክት ይህ ንጉሥ በኹለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ሞተም ከርሱም በኋላ ሌላ ከሀዲ ክፉ የኾነ ዲዮቅልጥያኖስ ነገሠ። እርሱም ክርስቲያኖችን በእጅጉ ያሳድዳቸውና ያሠቃያቸው ነበር። ይህም አባ ፊልክስ የክርስቲያኖችን ሥቃይ እንዳያይ ክብር ይግባውና ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። ቸሩ አምላክም ጸሎቱን ሰማውና በዲዮቅልጥያኖስ በመጀመሪያው ዘመነ መንግሥቱ አረፈ።

  + ይህም አባት ብዙዎች ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደርሷል፣ ከእርሳቸውም ስለውግዘትና ስለቀናች ሃይማኖት የተመላለሱበት አለ፣ እሊህም ለክርስቲያን ወገን እጅግ የሚጠቅሙ በጎዎች ናቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በጸሎቱ ይማረን፣ በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለፊልክስ ሊቀ ጳጳሳት ዘተኀርየ
ሶበ ፈከረ ሐዲሰ ወአጰንገለ ብሉየ
ኲነኔ ክርስቲያን ኢይርአይ በከመ ጸለየ
ወእምቅድመ ይምክር ላዕሌሁ ዲዮቅልጥያኖስ እኩየ
ሐዋዘ ሰከበ ወኖመ ጥዑየ።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት  #የአባ_ፍሞስ #የለንዲዎስ #የይላጥስ #የማርትሮስ #የኢላስዎስ #የቆርናልዮስ #የሱኪሮስ #የናውኔኖስ #የሊባዲቆ #የሲላስዮስና #የሰማዕት_ኤስድሮስ ማኅበር የኾኑት የሁለት መቶ ሰባ ኹለት ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን፣ በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ለቅድትስ ሰሎሜ ለቅዱስ ዮሳ ለቅዱስ ፊልክስ ሊቀ ጳጳሳት ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን።

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።

ዓርብ 13 ኖቬምበር 2020

+ በቅዱስ የተጻፈ የቅዱስ ገድል +

የምንኩስና ሕይወት ፋና ወጊ : የብዙ ብሒላት ተጠቃሽ : የበረሃው ኮከብ ቅዱስ እንጦንስ በምንኩስና የዘር ሐረግ ቀዳሚ ቢሆንም በሚገባው ልክ ያልተዘከረ የቤተ ክርስቲያን መብራት ነው:: በሀገራችን የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስቀድሞ በስሙ የታነጸ ቤተ ክርስቲያን እንደነበረና በኁዋላ የእመቤታችን ስም እንደ ጎላም ታሪክ ያስረዳናል:: 

የቅዱስ እንጦንስ ታሪክ ወንድማችን ዲያቆን መልአኩ ይፍሩ Melaku Yifru Zewulude Birhan ተርጉሞ አቅርቦልናል:: የመጽሐፉ ጸሐፊ ራሱም ሌላ ብዙ ገድል ያለው  የኢትዮጵያዊያን የቆብ አባታችን ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ነው:: ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ እንደ ቅዱስ እንጦንስ ያሉ አበውንና እንደ ቅድስት ሲንቀለጢቃ ያሉ እማትን ገድላት በመጻፍ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዕረፍት የለሽ ምርጥ ዕቃዋ መሆኑን አሳይቶአል:: ይህንን ጥንታዊ ተጠቃሽ መጽሐፍ ወንድማችን ደክሞ አበርክቶልናል:: ገዝተን ተሳልመን እናንብብ!

From: ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

የኅዳር ፭ ዝክረ ቅዱሳን።

እንኳን #ለቅዱስ_ለንጊኖስ_ሰማዕት እና #ለቅዱስ_ተባ_ዮሐኒ_ጻድቅ፣ ለሌሎቹም ንዑዳን ክቡራን ክብረ በዓላት በሰላም አደረሳችሁ።

የኅዳር ፭ ዝክረ ቅዱሳን። 

በዲያቆን መልአኩ ይፍሩ
----------------------------------------------------------------

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

¶ አመ ፭ ለኅዳር በዛቲ ዕለት፥ ኮነ አስተርእዮተ ርእሱ #ለቅዱስ_ለንጊኖስ ዘረገዘ ገቦሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት እንዘ ቊሱል ዲበ ዕፀ መስቀል።

✍️፩-ኅዳር ፭ በዚህች ዕለት ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሳለ ጐኑን የወጋ #የቅዱስ_ለንጊኖስ ራሱን የታየችበት ነው።

  + ይህም ቅዱስ በጌታችን ከአመነ በኋላ በቀጰዶቅያ አገር የጌታችንን ወንጌል በማስተማር ብዙዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሰ። በዚህም ግብሩ የቀኑ ክፉዎች አይሁድና አረማውያን ተነሡበት። በሐሰትም ወንጅለው በቀጰዶቅያ ራሱን አስቆረጡት። ራሱንም ብቻ ቆርጠው ወደ ኢየሩሳሌም አመጡ። ኋላም ከከተማ ውጪ አውጥተው ከአንድ ተራራ ላይ ቀበሩት። 

  + ከብዙም ቀናት በኋላ እንዲህ ኾነ። አንዲት በቅዱስ ለንጊኖስ ስብከት ያመነች ሴት በቀጰዶቅያ ትኖር ነበረች። ቅዱሱም ራሱን ከተቆረጠባት እለት አንስታ ስለርሱ እጅግ እያዘነች ታለቅስ ነበር። የእግዚአብሔርም ተአምር ሊገለጥ ስለወደደ ዐይኖቿ ታወሩ። ልጇም ይዞ እየመራት ወደ ኢየሩሳሌም፣ የጌራችንን መካናት ለመሳለምና ለመዳን ነበር። ኢየሩሳሌም እንደደረሰች ግን ልጇም ሞተና በሐዘን ላይ ጽኑዕ ሐዘን ደርሶባታልና እጅግ አዘነች። በዚህም ሐዘን ሳለች እንቅልፍ መጥቷት ተነኛች፣ በሕልሟም ቅዱስ ለንጊኖስንና ልጇን አየቻቸው። ቅዱስ ለንጊኖስም ሥጋውን ከዚያ ቦታ እንድታወጣ ነገራት። ከእንቅልፏም በነቃች ጊዜ ስለቦያው ጠየቀችና አገኘቸው። ቦታውም ሲቆፈር እጅግ ጥዑም የሽቱ መዓዛ ሸተተ። የቅዱስ ለንጊኖስን እና የልጇን ሥጋ ወደ አገሯ ወሰደቻቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፣ እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን፣ ለዘላለሙ አሜን።

ሰላም ለለንጊኖስ ዘተተክለ በሮም
ወተቀብረ ውስተ ወግር ዘኢየሩሳሌም
እንዘ ምስሌሁ ኅቡረ ወልዳ ንዉም
ከመ ተናገረ ለብእሲት በሕልም
ምስለ ጼና ዕፍረት ርእሱ አስተርአየት ዮም።

✍️፪-ዳግመኛም በዚህች ዕለት #የሰማዕት_ጢሞቴዎስ መታሰቢያው ነው፣ የሠራዊት አለቃ #ቅዱስ_ቴዎድሮስም ከሀገረ አትሪብ ወደ ሀገረ አስዩጥ ሥጋው የፈለሰበት ቤተ ክርስቲያኑም የከበረችበት ነው።

✍️፫-ዳግመኛም በዚህች ዕለት ወደ ብሔረ ሕያዋን የገባ #የአባ_ዮሐኒ መታሰቢያው ነው።

ሰላም ለከ ጢሞቴዎስ ቡሩክ
ሰማዕተ አምላክ
ብእሲ ሰማያዊ ወምድራዊ መልአክ
ኅብአኒ በክነፊከ በዕለተ ምንዳቤ ወሀውክ
እምነ ልሳን ምዑክ ወእምዐይን ድሩክ።

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋከ ቴዎድሮስብማር
አመ ኃሙሱ ለወርኃ ኅዳር
ሶበ በማዕበላ ፈቀደት አጥፍኦታ ለምድር
ሰሚዓ ትእዛዘከ ፈለሰት ባሕር
ቃለ እግዚኡ ከመ ይሰምዕ ገብር።

ሰላም እብል ለዘኮነ ሱቱፈ
ምስለ እለ ገብሩ ሰብእ ብሔረ ሕያዋን ምዕራፈ
እምሥርዓተ መላእክት ዮሐኒ ምንተኒ ኢያትረፈ
ከመ ሕይወቶሙ ሕይወተ ተጸገወ ዘልፈ
ወከመ ክንፎሙ አብቈለ አክናፈ።

(ምንጭ፥ ስንክሣር ዘወርኃ ኅዳር)
----------------------------------------------------------------
ወልደ ዳዊት ወልደ አብርሃም ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው በእንተ ቅዱስ ለንጊኖስ ወበእንተ ቅዱስ ቴዎድሮስ ወቅዱስ ጢሞቴዎስ ወበእንተ ቅዱስ አባ ዮሐኒ ወበእንተ ኲሎሙ ቅዱሳን እለኮነ ተዝካረ በዓሎሙ በይእቲ እለት መሐረነ ለነ ለአባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ አሜን። 

እግዚኦ ተዘከር ኪዳን ዘወሀብኮሙ ለቅዱሳን አግብርቲከ ወአእማቲከ እለ አስመሩ ኪያከ፣ ወሶበ ተዘከርከ ዘንተ ተዘከር ከመ መሬት ንሕነ አባስያን አግብርቲከ ወአእማቲከ፣ ኢታርእየነ ሙስናሃ ለቅድስት ሀገሪትነ ኢትዮጵያ ወለቅድስት ቤተ ክርስቲያን።  ኢታጥፍአነ ተዘኪረከ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሳህልከ እግዚኦ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።