ማቴ4፡8”ወእምዝ ነሥኦ ዲያብሎስ ወአእረጎ ውስተ ደብር ነዋኅ- ከዚህም በኋላ ወደረጅም ተራራ አወጣው”
ትርጓሜ ቅዱስ ወንጌል እንደሚነግረን የሰይጣንን የልቡና ፍቃድ ዐውቆ ሄደለት እንጂ እርሱስ የሚወስደው ሁኖ አይደለም። “ነገሥታትን ድል በማልነሳበት በቤተመቅደስ ቢሆን ድል ነሣኝ እንጂ ነገሥታትን ድል በምነሳበት በተራራ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ ነበር” ብሎ ማሰቡን ዐውቆ ሄደለት።
“ወአርአዮ መንግሥታተ ኲሉ ዓለም ወኲሉ ክብሮ- የዓለምን ሁሉ መንግሥታት ክብራቸውንም ሁሉ አሳየው”
† ጠጠሩን ወርቅ ብር ቅጠሉን ግምጃ አስመስሎ አሳየው።
† አንድም “መንግሥታተ ኲሉ ዓለም” ግዛቱን ሁሉ አሳየው “ወኲሎ ክብሮ” እንስሳት አራዊቱን ፈረስ በቅሎ ሠራዊት አስመስሎ አሳየው።
ሰይጣን ምንግዜም ቢሆን ውሸታምና የሌለውን አለኝ እያለ የሚያታልል ቀጣፊ ነው። በተአምረ ማርያም ላይ የነበረውን አንድ ነጋዴ እናስታውስ። እጅግ ሃብታም የነበረ አንድ ነጋዴ ነበር። በአንድ ወቅት ግን ንብረቱ ጠፍቶበት አዝኖ ተክዞ በመንገድ መጓዝ ጀመረ። ሰይጣንም ከመንገድ ቆየውና ምን ያስተክዝሃል ቢለው ያለኝ ሁሉ ማስኖብኛል ስለዚህ አዝኛለሁ አለው። ሰይጣንም መልሶ ታዲያ ወደየት ትሄዳለህ አለው። ከእንግዲህ ወዲህስ ከብሬ በነበርኩበት አገር ተዋርጄ ሰጥቼ በኖርኩበት ሀገር ተመጽውቼ አልኖርም ብዬ ወደሌላ ሀገር እየተሰደድሁ ነው አለው።
ሰይጣንም ድንጋዩን ወርቅ አድርጎ አሳየውና ይህን ብሰጥህስ አለው። እርሱም እሺ አለና ተቀበለ። ሰይጣን ግን ተንኮሉን አስከተለ። ነገር ግን አንድ ነገር ልታደርግልኝ እወዳለሁ አለው። ከዚያም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስን አምላክ አይደሉም ብለህ ካድልኝ አለው ካደለት፤ ዳግመኛም ቅዱሳንን ሁሉ ካድልኝ አለው። እርሱም ከዚያ ተወውና መመለስ ሲጀምር ቆየኝ አንድ ነገር ቀርቶኛል አለውና ከዚያ “ክርስትያኖች መመኪያችን የሚሏት አለችና እርሷን ካድልኝ” አለው። ያ ሰው ግን ይህንስ አላደርግም አለው። ሰይጣንም እርሷንማ ካልካድክ አምጣ አለና ለውጦ የሰጠውን ደንጊያ መልሶ በርሱ ልቡን ብሎ ገድሎታል። ከዚህ በኋላ ይህ ሰው በአቊራሪተ መዐት ምልጃ በመድኃኒታችንም ቸርነት ሊድን ችሏል። ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ፦
ቁ፦9 “ወይቤሎ ዘንተ ኲሎ እኁበከ እም ከመ ሰገድከ ሊተ ወአማኅከኒ- ብትሰግድልኝና እጅ ብትነሳኝ ይህ ሁሉ እሰጥኃለሁ አለው”
† ልብ በሉ ወዳጆቼ፤ ሰይጣን የቱን ያህል ደፋር እንደሆነ እናስተውል። ሠራዔ ኲሉ የሆነውን አምላክ ስገድልኝና ይህን ልስጠህ አለው። እንደምን ያለ ድፍረትና ትዕቢት ነው።
† መጽሀፈ አክሲማሮስ ይህን የሰይጣንን ትዕቢትና ድፍረት ሲነግረን መላእክት ሲያመሰግኑ እርሱ ዝም አለ
አያመሰግንም። መላእክትም ምነው አታመሰግንም አሉት እርሱም ደፋር ነውና ምን አደረገልኝ ብዬ አመሰግናለሁ። እናንተ ስታመሰግኑ ዐራተኛ እኔን አድርጋችሁ አመስግኑኝ አላቸው።
† በአንድ ጊዜም ለርሱ የወገኑትን መላእክት ከነርሱ ዐራት እንደኪሩብ መርጦ ተሸከሙኝና በሉ ኑ ተነስተን እግዚአብሔርን እንውጋ ብሎ ወደ ሰማይ መውጣት ጀመረ። እግዚአብሔር የልቡን የክፋት ጽናት ተመለከተና ከሰማይ ወደሰማይ ዝቅ እያደረገ ቢያወርደው ጽርሐ አርያምም ብትርቀው እርሱ ግን “እዩ አምላካችሁ አርያሙን ጠቅልሎ ሸሸ” ብሎ ተናገረ።(ሎቱ ስብሐት)
ቁ፦10 “ወእምዝ ይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ሑር እምኔየ ሰይጣን- ከዚህም በኋላ ጌታ ኢየሱስ ሂድ አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ወግድ አለው”
† ይህ አቡሃ ለሐሰት የሆነው ሰይጣን አሁን የመጣው ለርሱ በማይገባው በእግዚአብሔር የመለኮታዊ ባሕርዩ ገንዘብ በሆነችው አምልኮት ነውና ወግድ አለው። ምክንያቱም እንዲህ ባለ አኳኋን እና አነጋገር የሚመጣ ባላጋራ ጽኑዕ ባላጋራ ነውና ጽኑዕ ባላጋራዬ ወግድ ሲለው ነው።
† “እምድኅሬየ” በማለትም ከኔ በኋላዬ በሚነሱ ከምእመናን ወግድላቸው ብሎ ሰደደልን።
ቁ፦11 “ወእምዝ ኀደጎ ዲያብሎስ- ከዚህ በኋላ ተወው”
ቅዱስ ሉቃስ እስከጊዜው [በአይሁድ አድሮ እስኪያሰቅለው] ተወው ብሎ ያቀናዋል።
† ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰይጣን በአፍቅሮ ንዋይ በመጣበት ጊዜ በጸሊአ ንዋይ ድል ነስቶታል።
† አፍቅሮ ንዋይ ማለት ገንዘብን አጥብቆ መውደድ ማለት ነው። ገንዘብን ከልክ ባለፈ መጠን መውደድ ለደኃራዊ ሞት[ዳግም ሞት] የሚዳርግ ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለማችን ላይ የብዙዎቹን ተወዳጅ ወንድሞቻችንን ሕይወት ሰይጣን መጫወቻው እያደረገው ያለው በዚህ መንገድ ነው።ትልቅ ትምህርት ይሆነን ዘንድ የሚከተለውን ታሪክ እንመልከት።
† በመጽሃፈ ስንክሣር ጥር 30 ላይ የምናገኘው ታሪክ ነው።
† አንድ ፎላ የሚባል ካህን ነበር። ይህ ካህን ይኖርበት የነበረው ዘመንና ቦታ ጣዖት የሚያስመልክ አረማዊ ንጉሥ የነገሰበት ነበር። በአንድ ወቅት ይህ ካህን በተለያየ ሁኔታ ሰብስቦት የነበረውን ገንዘብ ንጉሡ ይወስድበታል። ካህኑም የተወሰደበት ገንዘብ እንዲመለስለት ይጠይቃል። ንጉሡ ግን ካህኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ ያስተማራቸውን እና ያሳደጋቸውን ሁለት ደናግል ለንጉሡ ጣዖት እንዲሠግዱ አሳምኖ ካመጣ እንደሚመልስለት ይነግረዋል።
† ካህኑም በፍቅረ ንዋይ ፈጽሞ ተነድፎ ነበርና ሄዶ እነዚያ ደናግል ለጣዖት እንዲሠግዱ ለማሳመን ብዙ ይጥራል። እነዚያ ደናግል ግን “ቀድሞ ለክርስቶስ ሥገዱ ብለህ አስተምረህን አሁን ደግሞ ለጣዖት ሥገዱ፤ ይህ እንደምን ይሆናል” ብለው እንደማይሰግዱ ነገሩት። ብዙ ቢሞክርም ስላልተሳካለት አስገድዶ ይዟቸው ወደ ንጉሡ ፊት ይዟቸው ቀረበ። ንጉሡም አሳመንሃቸው ብሎ በጠየቀው ግዜ እንዳልቻለ ገለጸለት።
† ንጉሥም ሦስቱም እንዲያዘ አዘዘ። ሁለቱም ደናግል ታሠሩ። ካህኑንም ገንዘቡን እንዳትሰጡት ብሎ አዘዘ። ደናግሉንም አሥረው ከመሰዊያው ቦታ አዘጋጇቸው። ንጉሡ ወደካህኑ ዘወር ብሎ መምህራቸው የሆነውን ያንን ካህን ልጆቹን እርሱ ራሱ ከቀላቸው ገንዘቡን እንደሚሰጡት ነገረው። ተወዳጆች ሆይ ይህ ምን ያህል የገንዘብ ፍቅር የሚያስከፍለውን ዋጋ ተመልከቱ። ይህም ካህን በፍቅረ ንዋይ ዐይነ ልቡናው ታውሮ ነበርና እኒያን ራሱ ስለክርስቶስ አስተምሮ ያሳደጋቸውን ምስኪን ደናግል በሰይፍ ቀላቸው። እነርሱም በገዛ መምህራቸው እጅ ሰማዕትነትን ተቀበሉ።
† ዳሩግን ንጉሡ ይህ ለገዛ ልጆቹ ያልራራ ለኔም ሊመለስ አይችልም ብሎ እርሱንም እዚያው በሰይፍ አስቀላው። እንግዲህ ተመልከቱ ይህ ካህን ወይ ከክህነቱ ወይ ከደናግል የመንፈስ ልጆቹ አለዚያም ከከንዘቡ አልሆነ በሰማይም ሳይጠቀም እንዳረፈ እንደዚያ እንዳይሆንብን እናስተውል።
† ገንዘብን እኛ ሠራነው እንጂ እርሱ አልሰራንምና ለመኖር ለቁመተ ሥጋ ስንል እንሥራ እንብላ እንጂ ኑሯችንን ሁሉ ለገንዘብ አሳልፈን አንስጥ። ከሞት በኋላ ስላለው ሕይወት ሁልጊዜም በማስተዋል እያሰብን እንራመድ።
ለጻድቅ አብርሃም ለጻድቅ እዮብ የሰጠውን ማስተዋል እና እምነት የቅዱሳኑ ሁሉ አምላክ ለሁላችንም ያድለን። አሜን።
ትርጓሜ ቅዱስ ወንጌል እንደሚነግረን የሰይጣንን የልቡና ፍቃድ ዐውቆ ሄደለት እንጂ እርሱስ የሚወስደው ሁኖ አይደለም። “ነገሥታትን ድል በማልነሳበት በቤተመቅደስ ቢሆን ድል ነሣኝ እንጂ ነገሥታትን ድል በምነሳበት በተራራ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ ነበር” ብሎ ማሰቡን ዐውቆ ሄደለት።
“ወአርአዮ መንግሥታተ ኲሉ ዓለም ወኲሉ ክብሮ- የዓለምን ሁሉ መንግሥታት ክብራቸውንም ሁሉ አሳየው”
† ጠጠሩን ወርቅ ብር ቅጠሉን ግምጃ አስመስሎ አሳየው።
† አንድም “መንግሥታተ ኲሉ ዓለም” ግዛቱን ሁሉ አሳየው “ወኲሎ ክብሮ” እንስሳት አራዊቱን ፈረስ በቅሎ ሠራዊት አስመስሎ አሳየው።
ሰይጣን ምንግዜም ቢሆን ውሸታምና የሌለውን አለኝ እያለ የሚያታልል ቀጣፊ ነው። በተአምረ ማርያም ላይ የነበረውን አንድ ነጋዴ እናስታውስ። እጅግ ሃብታም የነበረ አንድ ነጋዴ ነበር። በአንድ ወቅት ግን ንብረቱ ጠፍቶበት አዝኖ ተክዞ በመንገድ መጓዝ ጀመረ። ሰይጣንም ከመንገድ ቆየውና ምን ያስተክዝሃል ቢለው ያለኝ ሁሉ ማስኖብኛል ስለዚህ አዝኛለሁ አለው። ሰይጣንም መልሶ ታዲያ ወደየት ትሄዳለህ አለው። ከእንግዲህ ወዲህስ ከብሬ በነበርኩበት አገር ተዋርጄ ሰጥቼ በኖርኩበት ሀገር ተመጽውቼ አልኖርም ብዬ ወደሌላ ሀገር እየተሰደድሁ ነው አለው።
ሰይጣንም ድንጋዩን ወርቅ አድርጎ አሳየውና ይህን ብሰጥህስ አለው። እርሱም እሺ አለና ተቀበለ። ሰይጣን ግን ተንኮሉን አስከተለ። ነገር ግን አንድ ነገር ልታደርግልኝ እወዳለሁ አለው። ከዚያም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስን አምላክ አይደሉም ብለህ ካድልኝ አለው ካደለት፤ ዳግመኛም ቅዱሳንን ሁሉ ካድልኝ አለው። እርሱም ከዚያ ተወውና መመለስ ሲጀምር ቆየኝ አንድ ነገር ቀርቶኛል አለውና ከዚያ “ክርስትያኖች መመኪያችን የሚሏት አለችና እርሷን ካድልኝ” አለው። ያ ሰው ግን ይህንስ አላደርግም አለው። ሰይጣንም እርሷንማ ካልካድክ አምጣ አለና ለውጦ የሰጠውን ደንጊያ መልሶ በርሱ ልቡን ብሎ ገድሎታል። ከዚህ በኋላ ይህ ሰው በአቊራሪተ መዐት ምልጃ በመድኃኒታችንም ቸርነት ሊድን ችሏል። ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ፦
ቁ፦9 “ወይቤሎ ዘንተ ኲሎ እኁበከ እም ከመ ሰገድከ ሊተ ወአማኅከኒ- ብትሰግድልኝና እጅ ብትነሳኝ ይህ ሁሉ እሰጥኃለሁ አለው”
† ልብ በሉ ወዳጆቼ፤ ሰይጣን የቱን ያህል ደፋር እንደሆነ እናስተውል። ሠራዔ ኲሉ የሆነውን አምላክ ስገድልኝና ይህን ልስጠህ አለው። እንደምን ያለ ድፍረትና ትዕቢት ነው።
† መጽሀፈ አክሲማሮስ ይህን የሰይጣንን ትዕቢትና ድፍረት ሲነግረን መላእክት ሲያመሰግኑ እርሱ ዝም አለ
አያመሰግንም። መላእክትም ምነው አታመሰግንም አሉት እርሱም ደፋር ነውና ምን አደረገልኝ ብዬ አመሰግናለሁ። እናንተ ስታመሰግኑ ዐራተኛ እኔን አድርጋችሁ አመስግኑኝ አላቸው።
† በአንድ ጊዜም ለርሱ የወገኑትን መላእክት ከነርሱ ዐራት እንደኪሩብ መርጦ ተሸከሙኝና በሉ ኑ ተነስተን እግዚአብሔርን እንውጋ ብሎ ወደ ሰማይ መውጣት ጀመረ። እግዚአብሔር የልቡን የክፋት ጽናት ተመለከተና ከሰማይ ወደሰማይ ዝቅ እያደረገ ቢያወርደው ጽርሐ አርያምም ብትርቀው እርሱ ግን “እዩ አምላካችሁ አርያሙን ጠቅልሎ ሸሸ” ብሎ ተናገረ።(ሎቱ ስብሐት)
ቁ፦10 “ወእምዝ ይቤሎ እግዚእ ኢየሱስ ሑር እምኔየ ሰይጣን- ከዚህም በኋላ ጌታ ኢየሱስ ሂድ አንተ ሰይጣን ከኋላዬ ወግድ አለው”
† ይህ አቡሃ ለሐሰት የሆነው ሰይጣን አሁን የመጣው ለርሱ በማይገባው በእግዚአብሔር የመለኮታዊ ባሕርዩ ገንዘብ በሆነችው አምልኮት ነውና ወግድ አለው። ምክንያቱም እንዲህ ባለ አኳኋን እና አነጋገር የሚመጣ ባላጋራ ጽኑዕ ባላጋራ ነውና ጽኑዕ ባላጋራዬ ወግድ ሲለው ነው።
† “እምድኅሬየ” በማለትም ከኔ በኋላዬ በሚነሱ ከምእመናን ወግድላቸው ብሎ ሰደደልን።
ቁ፦11 “ወእምዝ ኀደጎ ዲያብሎስ- ከዚህ በኋላ ተወው”
ቅዱስ ሉቃስ እስከጊዜው [በአይሁድ አድሮ እስኪያሰቅለው] ተወው ብሎ ያቀናዋል።
† ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰይጣን በአፍቅሮ ንዋይ በመጣበት ጊዜ በጸሊአ ንዋይ ድል ነስቶታል።
† አፍቅሮ ንዋይ ማለት ገንዘብን አጥብቆ መውደድ ማለት ነው። ገንዘብን ከልክ ባለፈ መጠን መውደድ ለደኃራዊ ሞት[ዳግም ሞት] የሚዳርግ ነው። በአሁኑ ሰዓት በዓለማችን ላይ የብዙዎቹን ተወዳጅ ወንድሞቻችንን ሕይወት ሰይጣን መጫወቻው እያደረገው ያለው በዚህ መንገድ ነው።ትልቅ ትምህርት ይሆነን ዘንድ የሚከተለውን ታሪክ እንመልከት።
† በመጽሃፈ ስንክሣር ጥር 30 ላይ የምናገኘው ታሪክ ነው።
† አንድ ፎላ የሚባል ካህን ነበር። ይህ ካህን ይኖርበት የነበረው ዘመንና ቦታ ጣዖት የሚያስመልክ አረማዊ ንጉሥ የነገሰበት ነበር። በአንድ ወቅት ይህ ካህን በተለያየ ሁኔታ ሰብስቦት የነበረውን ገንዘብ ንጉሡ ይወስድበታል። ካህኑም የተወሰደበት ገንዘብ እንዲመለስለት ይጠይቃል። ንጉሡ ግን ካህኑ ከልጅነታቸው ጀምሮ ያስተማራቸውን እና ያሳደጋቸውን ሁለት ደናግል ለንጉሡ ጣዖት እንዲሠግዱ አሳምኖ ካመጣ እንደሚመልስለት ይነግረዋል።
† ካህኑም በፍቅረ ንዋይ ፈጽሞ ተነድፎ ነበርና ሄዶ እነዚያ ደናግል ለጣዖት እንዲሠግዱ ለማሳመን ብዙ ይጥራል። እነዚያ ደናግል ግን “ቀድሞ ለክርስቶስ ሥገዱ ብለህ አስተምረህን አሁን ደግሞ ለጣዖት ሥገዱ፤ ይህ እንደምን ይሆናል” ብለው እንደማይሰግዱ ነገሩት። ብዙ ቢሞክርም ስላልተሳካለት አስገድዶ ይዟቸው ወደ ንጉሡ ፊት ይዟቸው ቀረበ። ንጉሡም አሳመንሃቸው ብሎ በጠየቀው ግዜ እንዳልቻለ ገለጸለት።
† ንጉሥም ሦስቱም እንዲያዘ አዘዘ። ሁለቱም ደናግል ታሠሩ። ካህኑንም ገንዘቡን እንዳትሰጡት ብሎ አዘዘ። ደናግሉንም አሥረው ከመሰዊያው ቦታ አዘጋጇቸው። ንጉሡ ወደካህኑ ዘወር ብሎ መምህራቸው የሆነውን ያንን ካህን ልጆቹን እርሱ ራሱ ከቀላቸው ገንዘቡን እንደሚሰጡት ነገረው። ተወዳጆች ሆይ ይህ ምን ያህል የገንዘብ ፍቅር የሚያስከፍለውን ዋጋ ተመልከቱ። ይህም ካህን በፍቅረ ንዋይ ዐይነ ልቡናው ታውሮ ነበርና እኒያን ራሱ ስለክርስቶስ አስተምሮ ያሳደጋቸውን ምስኪን ደናግል በሰይፍ ቀላቸው። እነርሱም በገዛ መምህራቸው እጅ ሰማዕትነትን ተቀበሉ።
† ዳሩግን ንጉሡ ይህ ለገዛ ልጆቹ ያልራራ ለኔም ሊመለስ አይችልም ብሎ እርሱንም እዚያው በሰይፍ አስቀላው። እንግዲህ ተመልከቱ ይህ ካህን ወይ ከክህነቱ ወይ ከደናግል የመንፈስ ልጆቹ አለዚያም ከከንዘቡ አልሆነ በሰማይም ሳይጠቀም እንዳረፈ እንደዚያ እንዳይሆንብን እናስተውል።
† ገንዘብን እኛ ሠራነው እንጂ እርሱ አልሰራንምና ለመኖር ለቁመተ ሥጋ ስንል እንሥራ እንብላ እንጂ ኑሯችንን ሁሉ ለገንዘብ አሳልፈን አንስጥ። ከሞት በኋላ ስላለው ሕይወት ሁልጊዜም በማስተዋል እያሰብን እንራመድ።
ለጻድቅ አብርሃም ለጻድቅ እዮብ የሰጠውን ማስተዋል እና እምነት የቅዱሳኑ ሁሉ አምላክ ለሁላችንም ያድለን። አሜን።
ይቆየን!
መላኩ ዘውሉደ ብርሃን
የካቲት 17-2009 ዓ ም
ጎንደር
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ