አስቀድመን በመግቢያው እ ንደተመለከትነው መድኅን አለም ኢየሱስ ክርስቶስ የሄደው ወደበረሃ ነበር። የሄደበትም ዋነኛ ምክንያት አዳም ከዚህች ዓለም በአፍአ በሆነች በገነት በሠለስቱ አርእስተ ኃጣውእ ድል ተነስቷልና ስለዚህ ጌታችንም ከዚህ ዓለም በአፍአ በሆነች በገዳም ድል ይነሳለት ዘንድ ወደ ገዳም ሄደ።
ዳግመኛም የመነኮሳት የባሕታውያን ተጋድሎአቸው ከዚህ ዓለም በአፍአ በሆነ በገዳም በበረሃ ነውና ተጋድሎአቸውን ይባርክላቸው ዘንድ ወደዚያ ሄደ።
ማቴ4፡2 ”ወጾመ አርብአ መዓልተ ወአርብአ ሌሊተ-አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ”
ሠራዔ ሕግ ነውና ጾምን የመጀመሪያ ሕግ አደረገ። መባልዕት የኃጣውዕ መሠረት እንደሆኑ ሁሉ የበጎ ምግባራት የትሩፋት ሁሉ መሠረት ጾም ናትና።
“እማ ለጸሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወለቅዓ አንብዕ ወጥንተ ኲሉ ገድል ሠናይት-የጸሎት እናት እና የአርምሞ እኅት የእንባም ምንጭ የሆነች የበጎ ተጋድሎ ሁሉ መሰረት ናት” እንዲል
አርባ መጾሙም አስቀድመው አበው ነቢያት አርባ ጹመው ነበርና ከዚያ ቢያተርፍ ወይም ቢያጎድል አይሁድ ምክንያት ፈላጊዎች ናቸውና ደገኛይቱን ሕገ ወንጌልን ከመቀበል ወደኋላ ባሉ ነበር።
አንድም ዛሬ እባብ አካሉ የደገደገበት እንደሆነ አርባ ቀን ከምግብ ተከልክሎ ይሰነብታል። ከዚያም በስቁረተ ዕፅ(በእንጨት ቀዳዳ)በስቁረተ እብንም ቢሉ(በደንጊያ ቀዳዳ) አልፎ ሲሄድ ተገፎ ይወድቅለታል ይታደሳል። እናንተም አርባ ብትጾሙተሐድሶተ ነፍስን ታገኛላችሁ ለማለት ነው።ፍጻሜው ግን አዳም በአርባ ቀኑ ያገኛትን ልጅነት አስወስዷት ነበርና ካሳ መካሱን ለመናገር ነው።
ተወዳጆች ሆይ እርሱ እንዲህ ማድረጉ ለኔ ይጥቀመኝ ይበጀኝ ብሎ አይደለም። ዳሩ ግን ለደካማዎቹ ልጆቹ ለእኛ ሠርቶ አብ ነት ይሆን ዘንድ ነው እንጂ። ስለዚህም እርሱንአብነት አድርገን ጾሙን በተገባ ክርስቲያናዊ ምግባር ልንጾም ያስፈልገናል።
ስስት
ማቴ4፡3 “ ወእምዝ ርኅበ-ከዚህም በኋላ ተራበ”
† አርባ ሌትና መዓልት ከጾመ በኋላ ተራበ ይለናል ቅዱስ ማቴዎስ። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ረኃቡን ቢራብም በበጎ ፍቃዱ በተዋሐደው ሥጋ ነው። እርሱ አምስት ሺህ ሕዝብ የመገበ በብሉይ ለእስራኤል ዘሥጋ መናን ከሠማይ ያወረደና የመገበ፤አዕዋፍን ሳይዘሩ ሳያጭዱ ሳያከማቹ እርሱ አኃዜ ኲሉ የሚመግባቸው ለሁሉ ፍጥረት አስተካክሎ የሚመግብ እርሱ አኃዜ ዓለማት በእራኁ እንደምን ተራበ ለዚህስ አንክሮ ልባዌ ይገባል።
“ወቀርበ ዘያሜክሮ-የሚፈትነውም ቀረበው”
† ፈታኝ የተባለ ዲያብሎስ ወደርሱ እንደምን ሊቀርብ ቻለ? ቀድሞውኑ በጾሙ ጊዜ ስለምን ወደርሱ አልቀረበም ያልከኝ እንደሆን ጾምስ ሰይጣንን ክፉኛ የምታርቀው ሰይፍ የምትከለክለው ቅጽር እንደሆነች ቅዱስ ዮሐንስአፈወርቅን ምስክር አድርጌ እነግርሃለሁ። ቀድሞ በጾሙ ጊዜ ወደርሱ ባለመቅረቡ ጾም እንዴት ፍቱን የጾር መድኃኒት እንደሆነከዚህ ላይ ልብ ይሏል።
† በረሃቡስ ጊዜ እንዴት አውቆ ሊቀርበው ቻለ ትለኝ እንደሆን ይህማ ተራብሁ ሲል ቢሰማው ፍሬ ሲሻ ቢመለከተው ገጹን አጸውልጎ ቢታየው እንደተራበ ተረድቶ ቀረበው። ተወዳጅ ሆይ በዚህም ሰይጣን አንተ የልብህን አሳብ አውጥተህ ካልነገርከው በቀር አሳብህን እንዳያውቅብህ እወቅ። አንተ በተናገርህ ጊዜ ግን መድከምህን እና የደከምህበትን ቦታ ስላወቀ በደስታ ፈትኖ እንዲጥልህ ልብ በል።ጌታም ይህን ትምህርት እንድንወስድ እና እንድናስተውል ተራበ።
ሰይጣንም ወደርሱ ቀርቦ “እመሰ ወልደ እግዚአብሄር አንተ በል ከመ እላ አዕባን ኅብስተ ይኩና-አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ደንጊያዎች እንጀራ ይሁኑ ብለህ እዘዝ አለው”
† ሰይጣን ይህን ፈተና ሲያመጣ አስቀድሞ ትርጓሜ ወንጌሉ እንደሚለን በተቀደደ ስልቻ ሁለ ትኩስ ዳቦ አስመስሎ ደንጊያዎችን ይዞ ነበር የቀረበው። የጠየቀውም ፦
እሺ ብሎ ቢያደርግ የሰይጣን ተአዛዚ አሰኘዋለሁ ብሎ ባያደርገው ደካማ አሰኘዋለሁ ብሎ
አንድም ቢያደርገው ሌላ ጾር እሻበታለሁ(ሌላ ፈተና አመጣበታለሁ) ባያደርገው ድካሙን አይቼ እገባበታለሁ ብሎ አስቦ ነበር።
† ወዳጆች ሆ ይ ዲያብሎስ ከየት አምጥቶ ወልደ እግዚአብሔር ከሆንክ አለው እንዴት አወቀ ትለኝ እንደሆን ቀድሞ በባህረ ዮርዳኖስ “ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር” ያለውን ሰምቶ ነው። ወዳጆቼ አምላካችን በነቢያቱ “ይፈትን ልበ ወኩልያተ” የተባለለት ማእምረ ኅቡአት ስለሆነ ይህን ሐሳቡን አውቆበት የመጣበትን የስስት ፈተና በትዕግስት እንዲህ በማለት ድል ነስቶልናል።
ማቴ4፡4 “ወአውስአ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎ ጽሑፍ ከመ አኮ በኅብስት ከመ ዘየሐዩ ሰብእ አላ በኲሉ ቃል ዘይወጽእ እም አፉሁ ለ እግዚአብሔር-እርሱም መልሶ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፏል ብሎ መለሰለት”
† ይህም ማለት እግዚአብሔር ዳን ያለው ይድናል ሙት ያለው ይሞ ታል ማለት ነው። ይከውም ይታወቅ ዘንድ ጌታችን አልአዛርን “አልአዛር ውጣ” በማለት አራት ቀን የሞ ላውን ሬሳ ቀስቅሷል። ዳግመኛም በስደቱ ጊዜ የዮሴፍ ልጅ ለእመቤታችን የሄሮድስ ወታደሮች እየመጡባቸው እንደሆነ በነገራት ጊዜ እመቤታችን ስትደነግጥ ጌታችን መልሶ “መልእክቱን መናገርህ በጎ አደረግህ ዳሩ ግን እናቴን ስላስደነገጥሃት እስክመጣ ድረስ ይህን ደንጊያ ተንተርሰህ ቆ የኝ” ብሎት ለፍሱን ከስጋው ለይቶ አሳርፎታል።
† ተወዳጆች ሆይ ስስት ያልተሰጡትን እና የማያገኙትን ነገር መሻት ነው። አዳም ከገነት እንዲወጣ ያደረገውም ዋነኛው አድኡ ፈተና ስስት ነው። ይህ ጾር ብዙዎቻችንን ከመንፈሳዊነት የሚያስወጣን ወንድምን ከወንድሙ አባትን ከልጁ ሀገርንም ከሀገር የሚያጣላእና እስከመጋደል የሚያደርስ ነው።
† ቃየል አቤልን እንዲገድለው ያደረገውም ዋነኛው ነገር ስስት ነው። የተሰጠኝ ይበቃኛል ብሎ ቢቀመጥ እና ለወንድሙ የተሰጠውን በማየት ባይመኝ ወንድሙን ወደመግደል ባልደረሰም ነበር። ስስት ብዙዎችን ከመንግስተ እግዚአብሔር እንዲለዩና እንዲጣሉ ያደረገ ታላቅ ጾር ነው። ዲያብሎስም በትዕቢት እንዲናገርና የሐሰት አባት እንዲባለ ያደረሰችው ስስት ናት።
አምላካችንም ይህን ጾር እንዴት ማሸነፍ እንዳለብንድል ነስቶ በመሥራት አሳይቶናል።
† ተወዳጆች ሆይ ያለኝ ይበቃኛል ማለትን እና ራስን እንዲህ ካለው ጾር በትዕግስት በመግዛት ብጾም እና በሥግደት መበጎሰም ዱሳት መጻህፍትን በማንበብ ልንዋጋው ያስፈልጋል።አምላከ ቅዱሳን ለቅዱሳኑ ሁሉ የሰጠውን የትዕግስት አዕምሮ እና ኃይልን ለሁላችንም ያድለን። የቅዱሳኑ ሁሉ እና የድንግል ማርያም ጸሎት አይለየን። አሜን
ዳግመኛም የመነኮሳት የባሕታውያን ተጋድሎአቸው ከዚህ ዓለም በአፍአ በሆነ በገዳም በበረሃ ነውና ተጋድሎአቸውን ይባርክላቸው ዘንድ ወደዚያ ሄደ።
ማቴ4፡2 ”ወጾመ አርብአ መዓልተ ወአርብአ ሌሊተ-አርባ መአልትና አርባ ሌሊት ጾመ”
ሠራዔ ሕግ ነውና ጾምን የመጀመሪያ ሕግ አደረገ። መባልዕት የኃጣውዕ መሠረት እንደሆኑ ሁሉ የበጎ ምግባራት የትሩፋት ሁሉ መሠረት ጾም ናትና።
“እማ ለጸሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወለቅዓ አንብዕ ወጥንተ ኲሉ ገድል ሠናይት-የጸሎት እናት እና የአርምሞ እኅት የእንባም ምንጭ የሆነች የበጎ ተጋድሎ ሁሉ መሰረት ናት” እንዲል
አርባ መጾሙም አስቀድመው አበው ነቢያት አርባ ጹመው ነበርና ከዚያ ቢያተርፍ ወይም ቢያጎድል አይሁድ ምክንያት ፈላጊዎች ናቸውና ደገኛይቱን ሕገ ወንጌልን ከመቀበል ወደኋላ ባሉ ነበር።
አንድም ዛሬ እባብ አካሉ የደገደገበት እንደሆነ አርባ ቀን ከምግብ ተከልክሎ ይሰነብታል። ከዚያም በስቁረተ ዕፅ(በእንጨት ቀዳዳ)በስቁረተ እብንም ቢሉ(በደንጊያ ቀዳዳ) አልፎ ሲሄድ ተገፎ ይወድቅለታል ይታደሳል። እናንተም አርባ ብትጾሙተሐድሶተ ነፍስን ታገኛላችሁ ለማለት ነው።ፍጻሜው ግን አዳም በአርባ ቀኑ ያገኛትን ልጅነት አስወስዷት ነበርና ካሳ መካሱን ለመናገር ነው።
ተወዳጆች ሆይ እርሱ እንዲህ ማድረጉ ለኔ ይጥቀመኝ ይበጀኝ ብሎ አይደለም። ዳሩ ግን ለደካማዎቹ ልጆቹ ለእኛ ሠርቶ አብ ነት ይሆን ዘንድ ነው እንጂ። ስለዚህም እርሱንአብነት አድርገን ጾሙን በተገባ ክርስቲያናዊ ምግባር ልንጾም ያስፈልገናል።
ስስት
ማቴ4፡3 “ ወእምዝ ርኅበ-ከዚህም በኋላ ተራበ”
† አርባ ሌትና መዓልት ከጾመ በኋላ ተራበ ይለናል ቅዱስ ማቴዎስ። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ረኃቡን ቢራብም በበጎ ፍቃዱ በተዋሐደው ሥጋ ነው። እርሱ አምስት ሺህ ሕዝብ የመገበ በብሉይ ለእስራኤል ዘሥጋ መናን ከሠማይ ያወረደና የመገበ፤አዕዋፍን ሳይዘሩ ሳያጭዱ ሳያከማቹ እርሱ አኃዜ ኲሉ የሚመግባቸው ለሁሉ ፍጥረት አስተካክሎ የሚመግብ እርሱ አኃዜ ዓለማት በእራኁ እንደምን ተራበ ለዚህስ አንክሮ ልባዌ ይገባል።
“ወቀርበ ዘያሜክሮ-የሚፈትነውም ቀረበው”
† ፈታኝ የተባለ ዲያብሎስ ወደርሱ እንደምን ሊቀርብ ቻለ? ቀድሞውኑ በጾሙ ጊዜ ስለምን ወደርሱ አልቀረበም ያልከኝ እንደሆን ጾምስ ሰይጣንን ክፉኛ የምታርቀው ሰይፍ የምትከለክለው ቅጽር እንደሆነች ቅዱስ ዮሐንስአፈወርቅን ምስክር አድርጌ እነግርሃለሁ። ቀድሞ በጾሙ ጊዜ ወደርሱ ባለመቅረቡ ጾም እንዴት ፍቱን የጾር መድኃኒት እንደሆነከዚህ ላይ ልብ ይሏል።
† በረሃቡስ ጊዜ እንዴት አውቆ ሊቀርበው ቻለ ትለኝ እንደሆን ይህማ ተራብሁ ሲል ቢሰማው ፍሬ ሲሻ ቢመለከተው ገጹን አጸውልጎ ቢታየው እንደተራበ ተረድቶ ቀረበው። ተወዳጅ ሆይ በዚህም ሰይጣን አንተ የልብህን አሳብ አውጥተህ ካልነገርከው በቀር አሳብህን እንዳያውቅብህ እወቅ። አንተ በተናገርህ ጊዜ ግን መድከምህን እና የደከምህበትን ቦታ ስላወቀ በደስታ ፈትኖ እንዲጥልህ ልብ በል።ጌታም ይህን ትምህርት እንድንወስድ እና እንድናስተውል ተራበ።
ሰይጣንም ወደርሱ ቀርቦ “እመሰ ወልደ እግዚአብሄር አንተ በል ከመ እላ አዕባን ኅብስተ ይኩና-አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ እነዚህን ደንጊያዎች እንጀራ ይሁኑ ብለህ እዘዝ አለው”
† ሰይጣን ይህን ፈተና ሲያመጣ አስቀድሞ ትርጓሜ ወንጌሉ እንደሚለን በተቀደደ ስልቻ ሁለ ትኩስ ዳቦ አስመስሎ ደንጊያዎችን ይዞ ነበር የቀረበው። የጠየቀውም ፦
እሺ ብሎ ቢያደርግ የሰይጣን ተአዛዚ አሰኘዋለሁ ብሎ ባያደርገው ደካማ አሰኘዋለሁ ብሎ
አንድም ቢያደርገው ሌላ ጾር እሻበታለሁ(ሌላ ፈተና አመጣበታለሁ) ባያደርገው ድካሙን አይቼ እገባበታለሁ ብሎ አስቦ ነበር።
† ወዳጆች ሆ ይ ዲያብሎስ ከየት አምጥቶ ወልደ እግዚአብሔር ከሆንክ አለው እንዴት አወቀ ትለኝ እንደሆን ቀድሞ በባህረ ዮርዳኖስ “ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር” ያለውን ሰምቶ ነው። ወዳጆቼ አምላካችን በነቢያቱ “ይፈትን ልበ ወኩልያተ” የተባለለት ማእምረ ኅቡአት ስለሆነ ይህን ሐሳቡን አውቆበት የመጣበትን የስስት ፈተና በትዕግስት እንዲህ በማለት ድል ነስቶልናል።
ማቴ4፡4 “ወአውስአ እግዚእ ኢየሱስ ወይቤሎ ጽሑፍ ከመ አኮ በኅብስት ከመ ዘየሐዩ ሰብእ አላ በኲሉ ቃል ዘይወጽእ እም አፉሁ ለ እግዚአብሔር-እርሱም መልሶ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፏል ብሎ መለሰለት”
† ይህም ማለት እግዚአብሔር ዳን ያለው ይድናል ሙት ያለው ይሞ ታል ማለት ነው። ይከውም ይታወቅ ዘንድ ጌታችን አልአዛርን “አልአዛር ውጣ” በማለት አራት ቀን የሞ ላውን ሬሳ ቀስቅሷል። ዳግመኛም በስደቱ ጊዜ የዮሴፍ ልጅ ለእመቤታችን የሄሮድስ ወታደሮች እየመጡባቸው እንደሆነ በነገራት ጊዜ እመቤታችን ስትደነግጥ ጌታችን መልሶ “መልእክቱን መናገርህ በጎ አደረግህ ዳሩ ግን እናቴን ስላስደነገጥሃት እስክመጣ ድረስ ይህን ደንጊያ ተንተርሰህ ቆ የኝ” ብሎት ለፍሱን ከስጋው ለይቶ አሳርፎታል።
† ተወዳጆች ሆይ ስስት ያልተሰጡትን እና የማያገኙትን ነገር መሻት ነው። አዳም ከገነት እንዲወጣ ያደረገውም ዋነኛው አድኡ ፈተና ስስት ነው። ይህ ጾር ብዙዎቻችንን ከመንፈሳዊነት የሚያስወጣን ወንድምን ከወንድሙ አባትን ከልጁ ሀገርንም ከሀገር የሚያጣላእና እስከመጋደል የሚያደርስ ነው።
† ቃየል አቤልን እንዲገድለው ያደረገውም ዋነኛው ነገር ስስት ነው። የተሰጠኝ ይበቃኛል ብሎ ቢቀመጥ እና ለወንድሙ የተሰጠውን በማየት ባይመኝ ወንድሙን ወደመግደል ባልደረሰም ነበር። ስስት ብዙዎችን ከመንግስተ እግዚአብሔር እንዲለዩና እንዲጣሉ ያደረገ ታላቅ ጾር ነው። ዲያብሎስም በትዕቢት እንዲናገርና የሐሰት አባት እንዲባለ ያደረሰችው ስስት ናት።
አምላካችንም ይህን ጾር እንዴት ማሸነፍ እንዳለብንድል ነስቶ በመሥራት አሳይቶናል።
† ተወዳጆች ሆይ ያለኝ ይበቃኛል ማለትን እና ራስን እንዲህ ካለው ጾር በትዕግስት በመግዛት ብጾም እና በሥግደት መበጎሰም ዱሳት መጻህፍትን በማንበብ ልንዋጋው ያስፈልጋል።አምላከ ቅዱሳን ለቅዱሳኑ ሁሉ የሰጠውን የትዕግስት አዕምሮ እና ኃይልን ለሁላችንም ያድለን። የቅዱሳኑ ሁሉ እና የድንግል ማርያም ጸሎት አይለየን። አሜን
የካቲት 12፤2009ዓም
መላኩ ዘውሉደ ብርሃን
ጎንደር
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ