ሉቃስ 1፡34 -37 “ ማርያምም መልአኩን። ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው። መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ እግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። ”
ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ የእመቤታችንን እና የመልአኩን ንግግር በጻፈበት ክፍል ስናነብ ከላይ የተጠቀሰውን ምንባብብ
እናገኛለን። ከአራቱ ወንጌላውያን መካከል ሦስቱ {ማቴዎስ፡ ማርቆስ፡ ሉቃስ} የጻፉት ወንጌል የሚያመሳስለው ነገር ቢኖርም
እንኳን አራቱም የየራሳቸው የሆነ ልዩ ጠባይ እና መገለጫም አላቸው።
ቅዱስ ሉቃስም በተለይም የጌታችንን ወልደ እጓለ እም ሕያውነት በስፋት በመግለጥ የጻፈ አባታችን ነው። በዚህም መጽሐፉ እመቤታችንን በቤተመቅደስ ሐርን ከወርቅ አስማምታ ስትፈትል መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነውን
ታላቅ የምሥራች አበሠራት።
እመቤታችንም የመውለድን ነገር በልቧ እንደሌለ፤ ልጅ የመውለድን ከልጅም የነገሥታት ንጉሥ የሆነውን እንደምትወልድ
ባበሠራት ግዜ “ወልድ ስለማላውቅ ” አይሆንልኝም ብላው ነበር። መልአኩ ግን ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንጅ ተግባረ ዕሩቅ ብእሲ ማለትም በግብረ ብእሲ ወብእሲት{በሴትና በወልድ ግብር} የሚሆን እንዳይደል ዳሩግን በመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንደሆነ
ነግሯታል።
ይህንንም ሲነግራት ከዚህ በፊት ያልተደረገ ኋላም የማይደረግ መሆኑን ስላስተዋለ በመጨረሻ ሥራው የእግዚአብሔር መሆኑን በመግለጥ ደመደመው።
የእመቤታችን ድንግልና እና በድንብልና መውለዷን ምን ልዩ ያደርገዋል?
ሀ/ የእመቤታችንን ድንግልና ልዩ የሚያደርገው ነገር
† ንጽሕተ ትንጹሐን ድንግል ማርያም ድንግልናዋ ሥጋዊ ብቻ አልነበረም፤ በሕሊናዋም ጭምር እንጂ። ይህንም
ከራሷ ንግግር በደንብ በማስተዋል ስንመለከት እናገኘዋለን።
“ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?” - በሕግ ተወስኖ ወይም ያለሕግ ግብረ ብእሲ ወብስሲት መፈጸም ከዚህ ቀደምም ሆነ በኋላ በሐሳቧ እንደሌለ በደንብ ያስገነዝበናል። ለዚህም የመጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ንግግር አጽንኦት ይሰጠናል።
“ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” {ሉቃ 1፡28}
† ዘለአለማዊ፤ የታተመ፤ የማይፈታ፤ ያልተፈታ ድንግልና በመሆኑ። ይህም ሕዝቅኤል በራእዩ {44፡1-3} እንደተመለከተው ሲናገር “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።” ማለት የተመለከተውን ነገር በፍጹም መደነቅ ጽፎልን እናገገኛለን።
† አምላክን ያስገኘ፡ በእግዚአብሔር የተወደደ ንጽሕናና ውበት ያለው ነውና፤
ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ “ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።” {መዝሙረ ዳዊት 45፥11} ውበት ብሎ የተናገረው የእማምላክን ሥነ ላህይ{የገጽ ውበት} ብቻ አልነበረም፤ እንደውም በዋናነት ንጽሐናዋን ነው እንጂ።
ከዚህ ድንግልና የተገኘው አምላክ ወሰብእ መቃብሩን ሳይከፍት እንደተዘጋ ከሞት ተነሳ፤ በዝግ ቤት ውስጠ ምንም ሳይከፍት ገባ {ዮሐ 20፡26} ፤ ምትሐትም እንዳይባል ቅዱስ ቶማስ ተጠግቶ ዳሰሰው። ከዚያም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ “ጌታዬ አምላኬም” ብሎ መሰከረ።
ለ/ የእመቤታችን በድንግልና መውለድ
† ከላይ የተናገርነውን ሁሉ ያደረገው አምላክ ስለልደቱ ቀድሞ ሲነገርለት፡-
“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” {ኢሳ 7፡14} ተብሎ ተነግሮለት ነበር።
ኢሳይያስ በትንቢቱ ራሱ ጌታ ስለሚሰጠን ምልክት ተናግሯል። ምልክቱ ምንድነው? ማነው ምልክቱንስ የሚሰጠን?
ራሱ ጌታ የሰጠው ምልክት እንዴት ያለ ነው?
o ስለዚህ ነገር የኢሳይያስን መጽሐፍ ስናነብ በዚሁ ቀድመን በጠቀስነው ምንባብ ላይ መልሱን ይሰጠናል፤ “ድንግል ትጸንሳለች” በማለት።
o ታዲያ የድንግል መጽነስ ምኑ ያስደንቃል? በዚህች ድንግል መጽነስ ላይ ልዩ የሆነ ነገር ከሌለው በቀር ኢሳይያስ ምልክት ብሎ ያውም ራሱ ጌታ የሚሰጠው ምልክት ብሎ ሊናገርለት እንዴት ይችላል?
o ይህ ምልክት ታላቅ ኃይል የተጎናጸፈ እና ፍጡራንን በእጅጉ ያስደነቀ እስኪሆን ድረስ ከዋክብት እንኳን ፤ ከልደቱ መካን {ሥፍራ} ርሑቅ የነበሩትን ሰብአ ሰገልን እየመሩ እስኪያጡ ድረስ ድንቅ የሆነ ምልክት ምንኛ ድንቅ ነው?
o “ወኃይለ ልዑል ይጼልለኪ፤ የልዑል ኃይልም ይጸልልሻል” ተብሎም በቅዱስ ገብርኤል ተነግሯል። ኃይለ ልዑል የጸለላት {የከለላት፤ የጋረዳት፤ የከለከላት} ከምን ይሆን?
ከማስኖተ ድንግልና
ንጽሕት አድርጎ በመጠበቅ {ከኃጣውእ ከለላት}
o ኤልሳቤጥም “ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብጽዕት ናት” ብላ ስለንጽሕናዋ፤ ጌታም ነቢያቱን በማስነሳት ያናገረላትን በመፈጸሙ ንዕድ ክብርት መሆኗን መሠከረች።
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እመቤታችን እማማቅድስት ድንግል በክልኤ ማርያም ወላዲተ አምላክ ከንጹሐን ይልቅ ንጽሕት የሆነች፤ በሕይወቷም ለኛ ታላቅ ምሳሌ የሆነችን፤ በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ወልዳ መድኃኒትን የሰጠችን ንጽሕት ናትና እርሷን በማክበር እንከብር ዘንድ ከቅዱሳኑ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን። የቅዱሳኑ ሁሉ እና የእማማ ጸሎት አይለየን። አሜን።
ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ የእመቤታችንን እና የመልአኩን ንግግር በጻፈበት ክፍል ስናነብ ከላይ የተጠቀሰውን ምንባብብ
እናገኛለን። ከአራቱ ወንጌላውያን መካከል ሦስቱ {ማቴዎስ፡ ማርቆስ፡ ሉቃስ} የጻፉት ወንጌል የሚያመሳስለው ነገር ቢኖርም
እንኳን አራቱም የየራሳቸው የሆነ ልዩ ጠባይ እና መገለጫም አላቸው።
ቅዱስ ሉቃስም በተለይም የጌታችንን ወልደ እጓለ እም ሕያውነት በስፋት በመግለጥ የጻፈ አባታችን ነው። በዚህም መጽሐፉ እመቤታችንን በቤተመቅደስ ሐርን ከወርቅ አስማምታ ስትፈትል መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦ ለሰው ልጆች ሁሉ የሆነውን
ታላቅ የምሥራች አበሠራት።
እመቤታችንም የመውለድን ነገር በልቧ እንደሌለ፤ ልጅ የመውለድን ከልጅም የነገሥታት ንጉሥ የሆነውን እንደምትወልድ
ባበሠራት ግዜ “ወልድ ስለማላውቅ ” አይሆንልኝም ብላው ነበር። መልአኩ ግን ይህ የመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንጅ ተግባረ ዕሩቅ ብእሲ ማለትም በግብረ ብእሲ ወብእሲት{በሴትና በወልድ ግብር} የሚሆን እንዳይደል ዳሩግን በመንፈስ ቅዱስ ሥራ እንደሆነ
ነግሯታል።
ይህንንም ሲነግራት ከዚህ በፊት ያልተደረገ ኋላም የማይደረግ መሆኑን ስላስተዋለ በመጨረሻ ሥራው የእግዚአብሔር መሆኑን በመግለጥ ደመደመው።
የእመቤታችን ድንግልና እና በድንብልና መውለዷን ምን ልዩ ያደርገዋል?
ሀ/ የእመቤታችንን ድንግልና ልዩ የሚያደርገው ነገር
† ንጽሕተ ትንጹሐን ድንግል ማርያም ድንግልናዋ ሥጋዊ ብቻ አልነበረም፤ በሕሊናዋም ጭምር እንጂ። ይህንም
ከራሷ ንግግር በደንብ በማስተዋል ስንመለከት እናገኘዋለን።
“ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል?” - በሕግ ተወስኖ ወይም ያለሕግ ግብረ ብእሲ ወብስሲት መፈጸም ከዚህ ቀደምም ሆነ በኋላ በሐሳቧ እንደሌለ በደንብ ያስገነዝበናል። ለዚህም የመጋቤ ሐዲስ ቅዱስ ገብርኤል ንግግር አጽንኦት ይሰጠናል።
“ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” {ሉቃ 1፡28}
† ዘለአለማዊ፤ የታተመ፤ የማይፈታ፤ ያልተፈታ ድንግልና በመሆኑ። ይህም ሕዝቅኤል በራእዩ {44፡1-3} እንደተመለከተው ሲናገር “ወደ ምሥራቅም ወደሚመለከተው በስተ ውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም፦ ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፥ ሰውም አይገባበትም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል።” ማለት የተመለከተውን ነገር በፍጹም መደነቅ ጽፎልን እናገገኛለን።
† አምላክን ያስገኘ፡ በእግዚአብሔር የተወደደ ንጽሕናና ውበት ያለው ነውና፤
ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ “ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና።” {መዝሙረ ዳዊት 45፥11} ውበት ብሎ የተናገረው የእማምላክን ሥነ ላህይ{የገጽ ውበት} ብቻ አልነበረም፤ እንደውም በዋናነት ንጽሐናዋን ነው እንጂ።
ከዚህ ድንግልና የተገኘው አምላክ ወሰብእ መቃብሩን ሳይከፍት እንደተዘጋ ከሞት ተነሳ፤ በዝግ ቤት ውስጠ ምንም ሳይከፍት ገባ {ዮሐ 20፡26} ፤ ምትሐትም እንዳይባል ቅዱስ ቶማስ ተጠግቶ ዳሰሰው። ከዚያም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ “ጌታዬ አምላኬም” ብሎ መሰከረ።
ለ/ የእመቤታችን በድንግልና መውለድ
† ከላይ የተናገርነውን ሁሉ ያደረገው አምላክ ስለልደቱ ቀድሞ ሲነገርለት፡-
“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።” {ኢሳ 7፡14} ተብሎ ተነግሮለት ነበር።
ኢሳይያስ በትንቢቱ ራሱ ጌታ ስለሚሰጠን ምልክት ተናግሯል። ምልክቱ ምንድነው? ማነው ምልክቱንስ የሚሰጠን?
ራሱ ጌታ የሰጠው ምልክት እንዴት ያለ ነው?
o ስለዚህ ነገር የኢሳይያስን መጽሐፍ ስናነብ በዚሁ ቀድመን በጠቀስነው ምንባብ ላይ መልሱን ይሰጠናል፤ “ድንግል ትጸንሳለች” በማለት።
o ታዲያ የድንግል መጽነስ ምኑ ያስደንቃል? በዚህች ድንግል መጽነስ ላይ ልዩ የሆነ ነገር ከሌለው በቀር ኢሳይያስ ምልክት ብሎ ያውም ራሱ ጌታ የሚሰጠው ምልክት ብሎ ሊናገርለት እንዴት ይችላል?
o ይህ ምልክት ታላቅ ኃይል የተጎናጸፈ እና ፍጡራንን በእጅጉ ያስደነቀ እስኪሆን ድረስ ከዋክብት እንኳን ፤ ከልደቱ መካን {ሥፍራ} ርሑቅ የነበሩትን ሰብአ ሰገልን እየመሩ እስኪያጡ ድረስ ድንቅ የሆነ ምልክት ምንኛ ድንቅ ነው?
o “ወኃይለ ልዑል ይጼልለኪ፤ የልዑል ኃይልም ይጸልልሻል” ተብሎም በቅዱስ ገብርኤል ተነግሯል። ኃይለ ልዑል የጸለላት {የከለላት፤ የጋረዳት፤ የከለከላት} ከምን ይሆን?
ከማስኖተ ድንግልና
ንጽሕት አድርጎ በመጠበቅ {ከኃጣውእ ከለላት}
o ኤልሳቤጥም “ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈጸማልና ያመነች ብጽዕት ናት” ብላ ስለንጽሕናዋ፤ ጌታም ነቢያቱን በማስነሳት ያናገረላትን በመፈጸሙ ንዕድ ክብርት መሆኗን መሠከረች።
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እመቤታችን እማማቅድስት ድንግል በክልኤ ማርያም ወላዲተ አምላክ ከንጹሐን ይልቅ ንጽሕት የሆነች፤ በሕይወቷም ለኛ ታላቅ ምሳሌ የሆነችን፤ በድንግልና ጸንሳ በድንግልና ወልዳ መድኃኒትን የሰጠችን ንጽሕት ናትና እርሷን በማክበር እንከብር ዘንድ ከቅዱሳኑ ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን። የቅዱሳኑ ሁሉ እና የእማማ ጸሎት አይለየን። አሜን።
ይቆየን!
ዲያቆን መላኩ ይፍሩ ዘውሉደ ብርሃን
ታህሳስ 13 ፤2009 ዓ/ም