" እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ" /ሉቃ 1፥19/
ውድ ኦርቶዶክሳውያን ወንድም እኅቶቼ እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ኢየሉጣን እና ቅዱስ ቂርቆስን ላዳነበት ዓመታዊ የንግሥ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
+ዛሬ በጅማ ሀገረ ስብከት ሥር ወደ ሚገኘው የናትሪ ደብረ ሠላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተክራቲያን ይዣችሁ ልሄድ ነው።
+ደጆችሽ አይዘጉ ባዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ ላይ ለአገልግሎት ከየሰንበት ትምህርት ቤቱ ተጋብዘን ተሳትፈን የነበረበት ልዩ ጉዞ ነበር። ከአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከተነሳን በኋላ በሰበታ አድርገን ጉዟችንን ወደ ጅማ ናትሪ ቅዱስ ገብርኤል አደረግን።
+የጉዞውም ሆነ የማኅበሩ መንፈሳዊ ዓላማ የተዘጉ አቢያተ ክርስቲያናትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማስከፈትና እነዚያንም አገልግሎት ማገልገያ መባዕ አጥተው ዳግመኛ እንዳይዘጉ ለማድረግ የታሰበ ነው።
+ይህን ዓላማ በማንገብ ጉዟችንን ስንጀምር ቀኑ ተቆጥቶ ያኮረፈ ይመስል ነበር። ሰማዩም ፊቱን አጥቁሮብን እንባውን እያነባ ነበር። ከቆይታዎች በኋላ ወልቂጤ ደርሰን የወልቂጤ ቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤልን ቤተክርስቲያንን ተሳለምንና ከጉዟችን ትንሽ እረፍተ ወስደን ዳግም መጓዛችንን ቀጠልን።
+ የደቡብን ልዩና እጅግ ማራኪ የተፈጥሮ ገጽታ እየተመለከትን በትዝብትም ብዙ አሰብን። ይህን የመሰለ ድንቅ ለምለም ተፈጥሮ ይዞ የሚራብ ሀገርን ማየት እጅግ ለማመን ይከብዳል። ለነገሩ የአባይንስ ልጅ ውሃ ጠምቶት የለ።
+ ጊቤን እንደተሻገርን የምናገኛት በጂማ ሃገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ አቢያተ ክርስቲያናት ውስጥ የምእራፈ ቅዱሳን አበልቲ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወገብረ መንፈስ ቅዱስ የአንድነት ገዳምን ለመሳለም ወረድን። ቤተክርስቲያኗ በታላቅ ተጋድሎ ውስጥ ካሉ አቢያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዷ ናት። በዚያም ቀጣይ ተተኪ የሚሆኑ የአብነት ደቀመዛሙርት ያሉበት የአብነት ትምህርት ቤትም ያለባት ሲሆን እሊህን ደቀመዛሙርት የሚያስተምሩ ጥቂት መነኮሳት አሉ።
+ ከዚያም አለፍ ብለን ባለፈው ዓመት ሰኔ 8 ቀን ኦርቶዶክሳውያን መምእመናን ሌሊት ለጸሎት ተነስተው ሲሄዱ በአካባቢው ባሉ አክራሪ ሙስሊም ወንድሞች በሰይፍ የተመቱበት ታላቅ የተጋድሎ ቦታ የሆነውን የቁምቢ ቅዱስ ሚካኤልን ለመሳለም ወረድን። ቦታው እውነትም የተጋድሎ እና ታላቅ ሰማዕትነትን የሚጠይቅ ቦታ መሆኑን በዓይኑ ያየ ምስክር የሚሆንበት ታላቅ የተጋድሎ ቦታ ነው።
+ በዚያ ተሳልመን ለእነዚያ ጽኑዓን የተጋድሎ ወንድሞች ማገዣ የሚሆን ገንዘብ ተሰባስቦ ከተሰጠ በኋላ ጉዟችንን ቀጠልን።ንዝህላልነትና ዝለት ለሚያጠቃን አገልጋዮች ሰንበት ተማሪዎች እንዲሁም ምእመናን ታላቅ ምሳሌ የሚሆኑን የተጋድሎ ወንድሞቻችን ናቸው።
+ ከዚያ አለፍ ብለን የዶቢ ቅዱስ መድሐኔዓለምን ለመሳለም ወረድን። የቦታውን ሁኔታ ለተመለከተው በተለይም ታሪኩን ከነዚያ የዋህ ምእመናን አንደበት ለሰማ ሰው ቦታው ያለበትን ተጋድሎና የቤተክርስቲያኗን ችግር በማየት እንባውን መቀጣጠር አይቻለውም።
+ በምእመናኑ ፍጹም ተጋድሎ ጸንቶ የቆመ በመብዓ እጥረት ምክንያት ለአገልግሎት የተቸገረ ቤተክርስቲያን ነው።ይህንን የተመለከተው ዐይናችን እንደምንም እንባውን ከሳግ ጋር እየታገለበት ከልብ በማዘን የቻልነውን መባዕ እና ስጦታ በመስጠት ጉዟችንን ወደ ተነሳንብተ መዳረሻ ወደ ናትሪ ቅዱስ ገብርኤል አደረግን። ናትሪ ከተማ እንደደረስን የከተማዋን ሁኔታ ሲመለከቱ ትንሽ ከተማ ስትሆን በእግዚአብሔር ቸርነት፡ በተጋድሏቸው ጽናት እና በመልአኩ እርዳታ ጸንተው የቆሙ ክርስቲያኖችን ይመለከታሉ።
+ በዚህ ሁኔታ የጅማ ሀገረ ስብከት ትልቅ ክርስቲያናዊ ተጋድሎ ያለበት በማንኛውም ሰዓት ሰማዕትነት በራችንን አንኳኩቶ የሚመጣበት ምእመናን በስጋት የሚኖሩበት ሁኔታ ያለ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።
+ወደ ቤተክርስቲያኑ ስንገባ የማኅበሩ አገልጋይ ወንድምና እኅቶቻችን እግራችንን በማጠብ ተቀበሉን። በዚህ ቤተክርስቲያን ውስጥ ማኅበሩ ፕሮጀክት ኤርጋሞታ ብሎ የሚጠራው በሀገሬው ቋንቋ የሚሰብኩ ደቀ መዛሙርትን የሚያፈራ የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት አለ። በዚህም ማኅበሩ ለቤተክህነት ከማስረከቡ በፊት 44 ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል። በአሁኑ ሰዓት ግን በቤተ ክህነት አመራር ሥር ነው።
+ማኅበሩ ሌላም ፕሮጀክት ናቡቴ ቁጥር 1 ብሎ የሚጠራው የንብ ማነብ እና የአትክልት ማልማት ሥራ ይሠራል። በዚህም ቤተክርስቲያኑን ራሱን ለማስቻል ያገዘ ፕሮጀክት ነው።
+ ቦታው በዙሪያም ባሉ ሙስሊም ወንድሞች የተከበበ ፈተና የበዛበት ነው። ይህን የማኅበሩን ሥራ ተመልክተን ማኅበሩን ያስፋልን በማለት በልባችን ከመረቅን በኋላ የማታው የአውደ ምሕረት መርኃ ግብር ቀጠለ።
መርኃ ግብሩም እንዳለቀ የማኅሌቱ ሥርዓት ተጀምሮ ከዚያ በረከት ተሳትፈን በዓለ ንግሡን በደመቀ ሁኔታ አከበርን።
+ ስለማኅበሩ እና ስለ ዓላማው ስለሚሠራቸውም ሥራዎች እንዲሁም እንዴት በማኅበሩ ሥራ መሳተፍ እንደሚቻል እንደአምላከ ቅዱሳን ፍቃድ በቀጣይ ጊዜ አካፍላችኋለሁ።
+ እነዚህን አቢያተክርስቲያናት እና ጽኑዓን የተጋድሎ ክርስቲያን ወንድሞች እንድናስባቸው እና በቀጣይ ዓመት ለመጎብኘት የድርሻችንንም ለመወጣት በመመኘት ማስታወሻዬን ልቋጭ።
አምላከ ቅዱሳን ከቅዱሳኑ ሁሉ ረድኤትና በረከት ይክፈለን። ይቆየን።
+ደጆችሽ አይዘጉ ባዘጋጀው መንፈሳዊ ጉዞ ላይ ለአገልግሎት ከየሰንበት ትምህርት ቤቱ ተጋብዘን ተሳትፈን የነበረበት ልዩ ጉዞ ነበር። ከአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከተነሳን በኋላ በሰበታ አድርገን ጉዟችንን ወደ ጅማ ናትሪ ቅዱስ ገብርኤል አደረግን።
+የጉዞውም ሆነ የማኅበሩ መንፈሳዊ ዓላማ የተዘጉ አቢያተ ክርስቲያናትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ማስከፈትና እነዚያንም አገልግሎት ማገልገያ መባዕ አጥተው ዳግመኛ እንዳይዘጉ ለማድረግ የታሰበ ነው።
+ይህን ዓላማ በማንገብ ጉዟችንን ስንጀምር ቀኑ ተቆጥቶ ያኮረፈ ይመስል ነበር። ሰማዩም ፊቱን አጥቁሮብን እንባውን እያነባ ነበር። ከቆይታዎች በኋላ ወልቂጤ ደርሰን የወልቂጤ ቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤልን ቤተክርስቲያንን ተሳለምንና ከጉዟችን ትንሽ እረፍተ ወስደን ዳግም መጓዛችንን ቀጠልን።
+ የደቡብን ልዩና እጅግ ማራኪ የተፈጥሮ ገጽታ እየተመለከትን በትዝብትም ብዙ አሰብን። ይህን የመሰለ ድንቅ ለምለም ተፈጥሮ ይዞ የሚራብ ሀገርን ማየት እጅግ ለማመን ይከብዳል። ለነገሩ የአባይንስ ልጅ ውሃ ጠምቶት የለ።
+ ጊቤን እንደተሻገርን የምናገኛት በጂማ ሃገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ አቢያተ ክርስቲያናት ውስጥ የምእራፈ ቅዱሳን አበልቲ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ወገብረ መንፈስ ቅዱስ የአንድነት ገዳምን ለመሳለም ወረድን። ቤተክርስቲያኗ በታላቅ ተጋድሎ ውስጥ ካሉ አቢያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዷ ናት። በዚያም ቀጣይ ተተኪ የሚሆኑ የአብነት ደቀመዛሙርት ያሉበት የአብነት ትምህርት ቤትም ያለባት ሲሆን እሊህን ደቀመዛሙርት የሚያስተምሩ ጥቂት መነኮሳት አሉ።
+ ከዚያም አለፍ ብለን ባለፈው ዓመት ሰኔ 8 ቀን ኦርቶዶክሳውያን መምእመናን ሌሊት ለጸሎት ተነስተው ሲሄዱ በአካባቢው ባሉ አክራሪ ሙስሊም ወንድሞች በሰይፍ የተመቱበት ታላቅ የተጋድሎ ቦታ የሆነውን የቁምቢ ቅዱስ ሚካኤልን ለመሳለም ወረድን። ቦታው እውነትም የተጋድሎ እና ታላቅ ሰማዕትነትን የሚጠይቅ ቦታ መሆኑን በዓይኑ ያየ ምስክር የሚሆንበት ታላቅ የተጋድሎ ቦታ ነው።
+ በዚያ ተሳልመን ለእነዚያ ጽኑዓን የተጋድሎ ወንድሞች ማገዣ የሚሆን ገንዘብ ተሰባስቦ ከተሰጠ በኋላ ጉዟችንን ቀጠልን።ንዝህላልነትና ዝለት ለሚያጠቃን አገልጋዮች ሰንበት ተማሪዎች እንዲሁም ምእመናን ታላቅ ምሳሌ የሚሆኑን የተጋድሎ ወንድሞቻችን ናቸው።
+ ከዚያ አለፍ ብለን የዶቢ ቅዱስ መድሐኔዓለምን ለመሳለም ወረድን። የቦታውን ሁኔታ ለተመለከተው በተለይም ታሪኩን ከነዚያ የዋህ ምእመናን አንደበት ለሰማ ሰው ቦታው ያለበትን ተጋድሎና የቤተክርስቲያኗን ችግር በማየት እንባውን መቀጣጠር አይቻለውም።
+ በምእመናኑ ፍጹም ተጋድሎ ጸንቶ የቆመ በመብዓ እጥረት ምክንያት ለአገልግሎት የተቸገረ ቤተክርስቲያን ነው።ይህንን የተመለከተው ዐይናችን እንደምንም እንባውን ከሳግ ጋር እየታገለበት ከልብ በማዘን የቻልነውን መባዕ እና ስጦታ በመስጠት ጉዟችንን ወደ ተነሳንብተ መዳረሻ ወደ ናትሪ ቅዱስ ገብርኤል አደረግን። ናትሪ ከተማ እንደደረስን የከተማዋን ሁኔታ ሲመለከቱ ትንሽ ከተማ ስትሆን በእግዚአብሔር ቸርነት፡ በተጋድሏቸው ጽናት እና በመልአኩ እርዳታ ጸንተው የቆሙ ክርስቲያኖችን ይመለከታሉ።
+ በዚህ ሁኔታ የጅማ ሀገረ ስብከት ትልቅ ክርስቲያናዊ ተጋድሎ ያለበት በማንኛውም ሰዓት ሰማዕትነት በራችንን አንኳኩቶ የሚመጣበት ምእመናን በስጋት የሚኖሩበት ሁኔታ ያለ መሆኑን መገንዘብ ይቻላል።
+ወደ ቤተክርስቲያኑ ስንገባ የማኅበሩ አገልጋይ ወንድምና እኅቶቻችን እግራችንን በማጠብ ተቀበሉን። በዚህ ቤተክርስቲያን ውስጥ ማኅበሩ ፕሮጀክት ኤርጋሞታ ብሎ የሚጠራው በሀገሬው ቋንቋ የሚሰብኩ ደቀ መዛሙርትን የሚያፈራ የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት አለ። በዚህም ማኅበሩ ለቤተክህነት ከማስረከቡ በፊት 44 ደቀ መዛሙርትን አፍርቷል። በአሁኑ ሰዓት ግን በቤተ ክህነት አመራር ሥር ነው።
+ማኅበሩ ሌላም ፕሮጀክት ናቡቴ ቁጥር 1 ብሎ የሚጠራው የንብ ማነብ እና የአትክልት ማልማት ሥራ ይሠራል። በዚህም ቤተክርስቲያኑን ራሱን ለማስቻል ያገዘ ፕሮጀክት ነው።
+ ቦታው በዙሪያም ባሉ ሙስሊም ወንድሞች የተከበበ ፈተና የበዛበት ነው። ይህን የማኅበሩን ሥራ ተመልክተን ማኅበሩን ያስፋልን በማለት በልባችን ከመረቅን በኋላ የማታው የአውደ ምሕረት መርኃ ግብር ቀጠለ።
መርኃ ግብሩም እንዳለቀ የማኅሌቱ ሥርዓት ተጀምሮ ከዚያ በረከት ተሳትፈን በዓለ ንግሡን በደመቀ ሁኔታ አከበርን።
+ ስለማኅበሩ እና ስለ ዓላማው ስለሚሠራቸውም ሥራዎች እንዲሁም እንዴት በማኅበሩ ሥራ መሳተፍ እንደሚቻል እንደአምላከ ቅዱሳን ፍቃድ በቀጣይ ጊዜ አካፍላችኋለሁ።
+ እነዚህን አቢያተክርስቲያናት እና ጽኑዓን የተጋድሎ ክርስቲያን ወንድሞች እንድናስባቸው እና በቀጣይ ዓመት ለመጎብኘት የድርሻችንንም ለመወጣት በመመኘት ማስታወሻዬን ልቋጭ።
አምላከ ቅዱሳን ከቅዱሳኑ ሁሉ ረድኤትና በረከት ይክፈለን። ይቆየን።
ፎቶ፡- ቀሲስ ቴዎድሮስ እሸቱ
-በኃይሉ ተስፋዬ
-በኃይሉ ተስፋዬ
©ዘዲያቆን መላኩ
ዲያቆን መላኩ ይፍሩ ዘውሉደ ብርሃን
ሐምሌ 19 /2009ዓ.ም
ጅማ/ ናትሪ
ሐምሌ 19 /2009ዓ.ም
ጅማ/ ናትሪ