ምንጭ፥ Paradise of the Holly Fathers by St Athenasius, vol 2, p323
አማርኛ ትርጉም፥ ዲ/ን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደ ብርሃን
አንድ ወንድም እንዲህ አለ" በአንድ ወቅት ማኅበረ መነኮሳቱ የታላቁን የትንሳኤል ክብረ በዓል ለማክበር ተሰባሰቡ፤ በገዳሙም፣ አባቶች በሙሉ ባሕታውያኑ እና ሌሎችም መነኮሳት እንዲሁም በማኅበሩ የተሰባሰቡት ታላላቆቹም አበው ኹሉ እንዲህ ተብለው ተጠየቁ። ' በመነኮሳት ላይ ከሚመጡት ፈተናዎች ኹሉ ታላቁ እና ከባዱ ፈተና የቱ ነው?' ኹላቸውም በአንድነት መነኲሴውን በአቱን ጥሎ እንዲወጣ ከሚያደርገው ጾር የሚበልጥ ከባድ ጾር እንደሌለና ይህንም ያሸነፉት እንደኾነ ሌሎቹ ኹሉ እንደሚቀሉ ተናገሩ። ይህንን አስረዳን"
አረጋዊውም አባት እንዲህ በማለት መለሰ " በበአት ኹኖ መንፈሳዊ ተጋድሎን መጋደል በዚያው ለመጽናት ተስፋን ይጨምራል፤ ዳሩ ግን ከበአት ተለይቶ መውጣት ፈጽሞ ተስፋ ከመቊረጥ ጋር አንድ ነው። በበአቱ መንፈሳዊ ተጋድሎን እያደረገ እና የበአቱን ጸጥታ ወዶ እስከቆየ ድረስ ጥቂት በጥቂት ወደፊት በየጊዜው አንድ በአንድ ደረጃ ከፍ ይላል። በጌታችንም ኹሉን ጾር ጨርሶ እንደሚያሸንፍ ተስፋ አለው። ስለዚህም በምላሹ እና በተጋድሎው ቅድስናን እና የክርስቶስን ጸጋ ገንዘብ ያደርጋል። ነገር ግን ሕይወት እጅግ ከባድ ኹናበት(ፈተና በዝቶበት) በአቱን ጥሎ ቢወጣ፣ ዓላማ የሌለው ጉዞንም ቢጓዝ ጾሮቹን ድል በማድረግና ታላላቅ መንፈሳዊ ሃብታትን (ቅድስናን) ገንዘብ በማድረግ ፈንታ ተስፋ ከመቊረጥ ከዚያም ከፍጹም ጥፋት (ውድቀት) ይደርሳል። ስለዚህም ዓላማ የለሽ ጉዞን የሚያመጣ (ከመአት የሚያስወጣ) ጾርን የመሰለ ሌላ ከባድ ጾር የለም በማለታቸው አበው በእውነት ተናገሩ"
©ዲያቆን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደብርሃን
14-07-2010 ዓ.ም
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ
አማርኛ ትርጉም፥ ዲ/ን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደ ብርሃን
አንድ ወንድም እንዲህ አለ" በአንድ ወቅት ማኅበረ መነኮሳቱ የታላቁን የትንሳኤል ክብረ በዓል ለማክበር ተሰባሰቡ፤ በገዳሙም፣ አባቶች በሙሉ ባሕታውያኑ እና ሌሎችም መነኮሳት እንዲሁም በማኅበሩ የተሰባሰቡት ታላላቆቹም አበው ኹሉ እንዲህ ተብለው ተጠየቁ። ' በመነኮሳት ላይ ከሚመጡት ፈተናዎች ኹሉ ታላቁ እና ከባዱ ፈተና የቱ ነው?' ኹላቸውም በአንድነት መነኲሴውን በአቱን ጥሎ እንዲወጣ ከሚያደርገው ጾር የሚበልጥ ከባድ ጾር እንደሌለና ይህንም ያሸነፉት እንደኾነ ሌሎቹ ኹሉ እንደሚቀሉ ተናገሩ። ይህንን አስረዳን"
አረጋዊውም አባት እንዲህ በማለት መለሰ " በበአት ኹኖ መንፈሳዊ ተጋድሎን መጋደል በዚያው ለመጽናት ተስፋን ይጨምራል፤ ዳሩ ግን ከበአት ተለይቶ መውጣት ፈጽሞ ተስፋ ከመቊረጥ ጋር አንድ ነው። በበአቱ መንፈሳዊ ተጋድሎን እያደረገ እና የበአቱን ጸጥታ ወዶ እስከቆየ ድረስ ጥቂት በጥቂት ወደፊት በየጊዜው አንድ በአንድ ደረጃ ከፍ ይላል። በጌታችንም ኹሉን ጾር ጨርሶ እንደሚያሸንፍ ተስፋ አለው። ስለዚህም በምላሹ እና በተጋድሎው ቅድስናን እና የክርስቶስን ጸጋ ገንዘብ ያደርጋል። ነገር ግን ሕይወት እጅግ ከባድ ኹናበት(ፈተና በዝቶበት) በአቱን ጥሎ ቢወጣ፣ ዓላማ የሌለው ጉዞንም ቢጓዝ ጾሮቹን ድል በማድረግና ታላላቅ መንፈሳዊ ሃብታትን (ቅድስናን) ገንዘብ በማድረግ ፈንታ ተስፋ ከመቊረጥ ከዚያም ከፍጹም ጥፋት (ውድቀት) ይደርሳል። ስለዚህም ዓላማ የለሽ ጉዞን የሚያመጣ (ከመአት የሚያስወጣ) ጾርን የመሰለ ሌላ ከባድ ጾር የለም በማለታቸው አበው በእውነት ተናገሩ"
©ዲያቆን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደብርሃን
14-07-2010 ዓ.ም
አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ