ቅዳሜ 15 ሴፕቴምበር 2018

+ + Clement of Alexandria on the perfect person

The Perfect Person's Rule of Life:

The perfect person does not only try to avoid evil. Nor does he do good for fear of punishment, still less in order to qualify for the hope of a promised reward.

The perfect person does good through love.

His actions are not motivated by desire for personal benefit, so he does not have personal advantage as his aim. But as soon as he has realized the beauty of doing good, he does it with all his energies and in all that he does.

He is not interested in fame, or a good reputation, or a human or divine reward.

The rule of life for a perfect person is to be in the image and likeness of God.

+ St. Clement of Alexandria
Source:- Ancient christian wisdom

ቅዳሜ 8 ሴፕቴምበር 2018

+ + + እግዚአብሔርን ስለመፍራት እና ዲያብሎስን ስላለመፍራት + + +

"እግዚአብሔርን ፍራ" አለኝ "ትእዛዛቱንም ጠብቅ። የእግዚአብሔርን ትእዛዛት በመጠበቅህ በምታደርገው ኹሉ ላይ ኃይልን ትጎናጸፋለህ፤ የምታደርጋቸውም ኹሉ ወደር አይገኝላቸውም። እግዚአብሔርንም በመፍራትህ ነገሮችን ኹሉ በሚገባ ታከናውናለህ። ትድን ዘንድ እንዲህ ያለውን መፍራት ነው ገንዘብ ማድረግ የሚገባህ። ዳሩ ግን ዲያብሎስን አትፍራ፤ በርሱ ዘንድ ምንም ኃይል የለውምና እግዚአብሔርን በመፍራትህ በርሱ ላይ ትሰለጥንበታለህ። ነገር ግን በርሱ ዘንድ ኃይል የሌለው ያ መፈራት ያለ'ው አይደለም(መፈራት የለውም) ፤ ዳሩ ግን በርሱ ዘንድ ድንቅ ኃይል ያለው እርሱ በእውነት ይፈ'ራ ዘንድ አለ'ው። ኃይል ያለው ኹሉ መፈራት አለውና። ኃይል የሌለው ግን በኹሉ ዘንድ የተናቀ ይኾናል። ስለዚህም የከፉ ናቸውና የዲያብሎስን ሥራዎች ኹሉ ፍራ፤ እግዚአብሔርን ስለምትፈራ እኒህን (የዲያብሎስ ሥራዎች) አታደርጋቸውም፤ ከእነርሱ ራስህን ትጠብቃለህ እንጂ። ፍርሐት ኹለት ወገን ነው።

ክፉ የኾነውን ሥራ እንዳትሠራ ብትሻ እግዚአብሔርን ፍራ( ስለዚህም) ክፉውን ሥራ አትሠራውም፤ ዳግመኛም መልካም ሥራን ለመሥራት ብትሻ እግዚአብሔርን ፍራ፤ ስለዚህም መልካሙን ሥራ ትሠራለህ። በዚህም እግዚአብሔርን መፍራት ብርቱ፣ ታላቅና ድንቅ ነው። ስለዚህም እግዚአብሔርን ፍራ እናም ለርሱ ትኖራለህ፤ በቻልኸው ኹሉ መጠን እርሱን ፍራ ትእዛዛቱንም ጠብቅ ለእግዚአብሔርም ትኖራለህ።" "ለምን" አልሁ እኔም። "ጌታዬ፣ ለእግዚአብሔር ይኖራሉ ያልኸው ትእዛዛቱን ጠብቀው ስለሚኖሩት ነውን?" እርሱም እንዲህ አለኝ። "ምክንያቱም" "ፍጥረታት ኹሉ እግዚአብሔርን ይፈሩታል፤ ነገር ግን ትእዛዛቱን ኹሉም አይጠብቁም። እርሱን እግዚአብሔርን የሚፈሩት እና ትእዛዛቱንም የሚጠብቁት እነዚያ ከእግዚአብሔር ጋር በሕይወት መኖር አላ'ቸው፤ ዳሩ ግን ትእዛዛቱን በማይጠብቁት ለነርሱ ግን ሕይወት የላቸውም።"

ምንጭ፥the Shepherd of Hermas, Book two, commandment seven
አማርኛ ትርጉም፥ ዲያቆን መልአኩ ይፍሩ

©ዘዲያቆን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደብርሃን
            መጋቢት 18-2010 ዓ.ም
            አዲስ አበባ/ ኢትዮጵያ