ሐሙስ 10 ሜይ 2018

ወላዲተ አምላክ በቅዱሳን አንደበት

ዲያቆን መልአኩ ይፍሩ ዘውሉደ ብርሃን:
" አሐቲ ይእቲ ለእማ ወኅሪት ይእቲ ለእንተ ወለደታ -
ለእናቷ አንዲት ናት ለወለደቻትም የተመረጠች ናት "

                                መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን

" ኦ ማርያም አኮ በፍትወተ ደነስ ዘአጸለስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ
- ማርያም ሆይ በኃጢአት በሆነ ፍትወት የተጸነሽ አይደለም በሕግ በሆነ ሩካቤ ከኢያቄም ከሐና ተወለድሽ እንጂ "
                                               ቅዱስ ሕርያቆስ

" ወኮንኪ ለነ ተንከተመ ለዕርገት ውስተ ሰማይ - ከምድር ወደ ሰማይ ለመውጣት መሰላል ሆንሽን "

                                               ቅዱስ ኤፍሬም

" መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን
ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን
እም ኲሉ ተአይኒሁ ለያእቆብ
መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራሮች ነው
ከያእቆብ ከተማ ሁሉ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች መርጧልና "
                                                ቅዱስ ዳዊት

" ማርያምሰ ተኀቱ ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባህርይ ጸአዳ - ማርያምማ በአዳም ባህርይ ውስጥ እንደ ነጭ(ጸአዳ እንቊ) ታበራ ነበር "
                                                ቅዱስ ያሬድ